Search This Blog

Saturday 3 September 2016

መፍትሄው ወይ ከትውልዱ መታረቅ አልያም መታነቅ
@@@@@@@@@@
ወንድ ናቸው!! ሳንፈልግ ጥቅልል አድርገው በብሄር ቋት ውስጥ ሊከቱን ትንሽ ቀራቸው። ሰው ከመሆን ተፈጥሯዊ ፀጋ ሰው ወደ አበጀው ብሄርተኝነት።ሰውነት ሊያከትም፣ እንደ መንጋ ግርርር እያልን የእንስሳዊነት ባህሪ ልንላበስ።ያን ግዜ እንደ ሰው ማሰብ ይቀራል። ሁሉም ለቡድኑ እና ለብሄሩ ብቻ ማሰብ ይጀምራል። ያ ትውልድ ይዞት የመጣው በሽታ። የ ያ ትውልድ አባሎች እናንተ የዚያን ትውልድ አድንቃችሁ አትጠግቡም። ለእኔ ትውልድ ያመጣችሁት አንዳችም ለውጥ ባለመኖሩ እና ይልቁንም በብሄር ቋት ውስጥ ልትከቱን ስለምትለፉ እኛ ስለምን እንውደዳችሁ? አሁን በስልጣን ላይ ያሉትም አብዛኞቹ የ ያ ትውልድ አባል ናቸው። ለዚያም ልንጣጣም አልቻልንም። እናንተ ታግለን የብሄር ብሄረሰቦችን መብት አስከበርን ትሉናላችሁ። እኛ ደግሞ የሰዎችን ወይም የግለሰቦችን መብት መቼ አስከበረችሁ ብለን እንሞግታለን። ቡድን ካለግለሰብ ይፈጠር ይመስል የቡድንን መብት ልትጨፈልቁ ነው የሚል ምላሽ ትሰጡናላችሁ። እናንተ የ ያ ትውልድ አባሎች በሰብዓዊ መብት አያያዝ በዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ምርጦች ነን ትሉናላችሁ። የእኔ ትውልድ አሁን ይችን እየፃፍኩ ባለበት ቅፅበት ስለ ዓለም ሃገራት የሰብዓዊ መብት አያያዝ የመረጃ መረብን ዘርግቶ ከሌሎች ሃገራት የእንስሳት መብት አያያዝ እንኳ እንደማንሻል ይነግራችኋል። ለምሳሌ
ጃፓን እንስሳትን ስለመቆጣጠር እና ስለመንከባከብ ባወጣችው ህጓ አንቀፅ 2 እንዲህ ይላል።
" All people must not only refrain from killing, injuring, and inflicting cruelty upon animals, but they must also treat animals properly, taking their natural habits into account." ይህንን እናንተ አትነግሩንም። እናንተ በአካል ምናልባትም ለልምድ ልውውጥ በሚል ሃገሩን ታውቁት ይሆናል። እኛ አለም በአንድ መንደር ስር ገብታለች ብለን የፈለግንውን አገር: ቤታችን ሆነን እንጎበኛለን። በጃፓን
ህግ ብቻ ወጥቶ አልቀረም። እንስሳት ላይ ጉዳት ያደረሰም የሚደርስበት ቅጣት ተወስኖ ተግባራዊ እየትተደረገ ነው።
(Penalties)
Article 13. Any person who cruelly treats or who abandons a protected animal shall be liable to a fine or minor fine of not more than thirty thousand yen (~30,000).
እኛ በህግ ደረጃ የምንታማ አይመስለኝም። ያወጣንውን ህግ የማይተገብር ተፈጠረና ህግ አውጪውን ህግ አክብር በሚል ፀብ ላይ ነን። የእኔ ትውልድ ከዚያ ትውልድ ጋር ያልተግባባው በአስተሳሰብ ልዩነት ነው። የ1960ዎቹን አስተሳሰብ ለእኔ ትውልድ ና ተጋት ብትሉት ሌላው ቀርቶ በንግግር እንኳ መግባባት ስለማይቻል ወደ አመፅ ይቀየራል። ችግሩ አመፁን በዚያው ዘመን እሳቤ በዱላ እናበርደዋለን ብላችሁ ታስባላችሁ።
በዚህ ወር ውስጥ በአማራ ክልል በተነሳው ተቃውሞ የሰው ህይወት ጠፍቷል። ከመንግስት ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት አላቸው የተባሉ ሰዎች ንብረት ጉዳት ደርሶበተል። ይህንን የሰው ህይወት መጥፋት ሰዎች(ከሰውነት ደረጃ የወረዱ እንበል ይሆን?) አንደኛው ወገን የትግራይ ተወላጆች ላይ በዘራቸው ጥቃት ደረሰባችው ብሎ እሪሪ ይላል። ሌላው ወገን ደግሞ አማራው እየተገደለ ነው ይላል። እውነቱ ግን በአካባቢው ሰዎች ላይ ጉዳት እየደረሰ መሆኑ ነው። ሰው እየተገደለ መሆኑ ነው። ስለምን "በሰዎች ላይ የሚወሰደው እርምጃ ይቁም" አላልንም። እዚያ ቦታ ከየትም ይምጣ ከየት ብቻ ሰው ይኖራል።ሰው ከመሆን የተፈጥሮ ፀጋ ወደ ሌላ ሰው ያለመሆን ክሰተት እየተጠፈጠፍን ነው።ከዚህ ካልወጣን እንቸገራለን። አብሮ ተዋልዶ የኖረን ለያይቶ ማቧደን መልሶ ሴራ ጠንሳሹን ነው የሚያጠፋው። እያየንውም ነው።ይቺ ሃገር አስማት ነች።ይሄን ህዝብም በጭራሽ አታውቁትም። አለያየንው ብለን ስንል እድር እና እቁብ ላይ ተሰብስቦ የምናገኘው። ተማርኩ ብሎ ከሚዘባርቀው ሰው እጥፍ የሞራል ልዕልና ያለው ህዝብ። እንኳን ስትሸጠው ስታስማማው የሚያውቅ ህዝብ። የማይሆን ነገር ስትሰራ ተሰልፎ ደግፎ፤ ተሰልፎ መቃብርክን የሚቆፍርልህ። ቢመክርህ ወይም ተው አይሆንም ቢልህ ልታጠቃው እንደምትችል ስለሚያውቅ ለምን ይመክርሃል? ጌታየ ህዝቡን ለማወቅ ጥልቅ የስነ ልቦና ጥናት የሚጠይቅ ነው። እናም ከሰውነት ስትወርድ በርታ እያለ የሚቀብርህ ራሱ ነው። አሁን መፍትሄው ወይ ከትውልዱ መታረቅ አልያም መታነቅ ነው።

Translate

About Me