Search This Blog

Saturday 16 July 2016

Maalan jira
መኪና ስላለህ በእግርህ ወይ በታክሲ አትሄድም አይደል? ትልቅ
ቪላ ቤትህ ውስጥ ብፌ ተዘጋጅቶ ስለምትመገብ አነስ ያሉ
ሆቴሎች እና ምግብ ቤቶች አትገባም አይደል? ግቢህ
ው�ስጥ እሳት አያይዘህ በግ አርደህ በውስኪ ስለምታወራርድ
አነስተኛ መጠጥ ቤቶች እና ጭፈራ ቤቶች አትገባም ይሆናል።
በቃ ተበድለሃል። የሰዎች ፍቅር ተነፍጎሃል። በዚህ ቅንጡ ኑሮህ
ውስጥ በመደበቅህ ወይም ታች ያለ ኑሮ በመናቅህ የሚገርም
ፍቅር አጥተሃል። የማያውቅህ ሰው ፍቅር። የማያውቅህ ሰው
ግፊያ እና ይቅርታ። በዚያውም ትውውቅ። በዚያው ጥልቅ
ወዳጅነት።ቢዚያው ችግሮቻቸውን ማወቅ እና ማየት።እስኪ
በሞቴ ከላይ የነገርኩህን ለአንድ ሳምንት እንኳ አድርገው። ቆይ
እንዲያውም እኔ አነስተኛ ጭፈራ ቤት ይዤህ ልግባማ። ደብረ ብረሃን ነው።ቤቷ
አነስተኛ ናት። ጥቅጥቅ ብላ ሞልታለች። ጥግ ጥግ ባንኮኒ ላይ
ተደግፈው ከሚጠጡት ውጪ ሁሉም ጨርቃቸውን ጥለው
ይጨፍራሉ። ይተቃቀፋሉ። አንዱ ጆሮውን አጎንብሶ ወደ ሌላኛው
ሰው አፍ አስጠግቶ ወሬ ይቀበልና ድጋሚ ያኛው ደግሞ
ጆሮውን ለዚያኛው ሰው ያቀብላል። እልፍ ብሎ የቢራ ጠርሙስ
ይጋጫል። ቺርስስስ! ይቺን አጭር ግዜ በደስታ ለማሳለፍ፤
ያለብንን የህይወት ውጣ ውረድ ለመርሳት፤ ከቤት፣ከሚስት
ወይም ከሌላ ሰው ለመሸሽ፤ ብስቶን ለመተንፈስ ወይ
ለመርሳት፤ብቻ ይጠጣለታል። ጥጉ በሙሉ በመያዙ የቢራየን
አንገት በእጄ አቅፌ ወደ መሃል ገባሁ። ካለ ውዝዋዜ መቆምና
መጠጣት የለም የተባለ ይመስል ቤቷ ወዲያ ወዲህ ትላጋለች።
አንዱ ሙዚቃ አልቆ ሌላው ሙዚቃ ሲገባ የጭፈራ ስልቱ
ተቀይሮ ሌላ ድባብ ይፈጠራል። እዚህ በየ ሰከንዱ ሙዚቃ
ብትቀይር የሚከስስህ የለም። የጭፈራ ስልት ይቀየራል እንጂ።
የሃጫሉ ሁንዴሳ "ማለንጅራ*" ተከፈተ። ያቺ ቤት ተርገበገበች።
ጨፋሪው ትከሻውን እያወዛወዘ መሬቱን በእግሩ እየመታ ቤቷ
እሪሪ ልትል ደረሰች። የዚያ ሁሉ ሰው ትንፋሽ ከመስተዋቱ ላይ
ጤዛ ሰርቶ "ጠብ" ይላል። ሰው ፊቱ ላይ እንደ ጎርፍ
የሚንቆረቆረውን ላብ በጃኬቱ እየጠረገ ያብዳል። በእጄ
የያዝኩትን ቢራ ስጎነጨው ከወትሮው ለየት ብሎ ጣፈጠኝ። ግን
ሞቋል። ያም ቢሆን ይጣፍጣል። ሙዚቃው ሲያልቅ አጣገቤ
ላብበላብ ሆኖ ሲጨፍር የነበረ ወጣት ወደ ጆሮየ ጠጋ ብሎ ደስ
በሚል ቅላፄ
"በናትህ ሙዚቃውን አስደግምልኝ። እኔ ኦሮሞ ነኝ።ዘፈኑን
እወደዋለሁ" አለኝ። ሄጄ ለሙዚቃ አጫዋቹ ሙዚቃውን
እንዲደግምልን ነገርኩት። ሃጫሉ ተደገመ። ልጁ በደስታ
ሰከረ።ድንገት ከአጠገቤ ተሰወረ። ዞር ዞር ስል የለም። ወዲያው
ከጀርባየ ያልተከፈተ ቢራ ታቅፎ መጣ። ጠርሙሳችንን አጋጨን።
አይደክመውም። ሙዚቃው እስከሚያልቅ ጨፈረ። ሌላ ሙዚቃ
ቀጠለ። ጎጃምኛ። ቤቷ አትቆምም። በማንኛውም ሙዚቃ
ይጨፈራል፤ ይጠጣል። በተጀመረው ሙዚቃ እየጨፈረ ያ ልጅ
በድጋሚ "በናትህ የሃጫሉን አስደግምልኝ" አለኝ።
አለመነታሁም። አስደገምኩለት። ለምን ተደገመ አይባልም። ብቻ
ያስጨፍር እንጂ እኔ ራሱ ተነስቼ ብዘፍን የሚቃወም የሚኖር
አይመስለኝም። ምክንያቱም ይህ ጭፈራ ቤት ነውና። ሙዚቃው
ሲጀምር ልጁ የጭፈራ እብደቱ ተነሳበት። እሱ ብቻ አይደለም።
ጭፈራ ቤቱ ውስጥ ያሉ ሁሉ አቧራ የለም እንጂ አቧራውን
አጨሱት። ሙዚቃው ሲያልቅ ወደ ባንኮኒው እየጎተተ ይዞኝ ሄዶ
ፍላጎቴን እንኳ ሳይጠይቀኝ "10 ቢራ ስጠው" ብሎ የ10 ቢራ
ከፍሎ በትከሻው ሰላም ብሎኝ ተጠባብቆ የሚጨፍረውን ሰው
በእጁ እየፈለፈለ ጥሎኝ ወጣ። ምክንያቱም ውስጡን
የሚያይበት ወይም ብሶቱን የሚረዳበትን ነገር አግዠዋለሁና
መሰለኝ!! እናማ ከዚህ በፊት በአይን እንኳ አላውቀውም። እናም
አልኩ። መኪናም ይኑርህ በእግርህም በታክሲም ተንቀሳቀስ።
የፈለገ ድሃ ባትወድ ግዴለም ይሄ ማህበረሰብ የሚውልበት ቦታ
ዋል። ክብሬ ምንትስ አትበል። በስራ ሰዓትህ የፈለገ ትልልቅ
የሃገር ጉዳይ ስታስፈፅም ዋል። ግን በእረፍት ግዜህ ብዙሃኑ
ወደሚውልበት ሂድ። መስሪያ ቤት አብሮህ የሚውል ሰው
ፈርቶህ አልያም የራሱ ጉዳይ ብሎ ስለ አንተ ላይነግርህ
ይችላል እዚህ ግን ሳያውቅ ስላንተ የሚባለውን ሁሉ
ይነግርሃል። ራስህንም ታይበታለህ። ከፈለክም በ6ወር አንዴ
ጥንብዝ ብለህ ስከር!! ብስቶህን ተንፍሰህ ትገላገልበታለህ!!!
ደርግ እንዴት ሊናፍቀን ይችላል? እንዴትም!!
(የመንግስቱን ፎቶ እየለጠፋችሁ ለምታዝጉን ሰዎች ይሁን)
@@@@@@@@@@@@
"....ጠዋት ሚያዝያ 19ቀን 1970 ዓ.ም
በግምት ከንጋቱ 12
ሰዓት ቤታችን ሆነን የተኩስ ድምፅ ሰማን።...በዚያኑ ቀን ወደ
ትምህርት ቤት ስሄድ ወንድሜ ወልደ አብ ደንቡ ተገድሎ
አሥከሬኑ ከቀበሌው ፅ/ቤት ፊትለፊት ካለ አስፓልት መንገድ
ላይ ተጥሎ አይቼ ዝም ብየ በማለፍ ትምህርት ቤት ገባሁ።.....
((ወደ አስከሬኑ(ተጨምቆ)) ከመሄዳችን በፊት በስልፉ ላይ አቶ
ታደሰ መንገሻ፣ ገ/ጊዮርጊስ ስራቱና እንድርያስ ቡታ ሆነው
ስሜን ጠርተው በማውጣት በታጣቂዎች ካስያዙን በኋላ
ለተማሪዎቹ 'የሰባት ቤት ጉራጌ ቀንደኛ መሪ የሆኑት
እነወልደአብ ደንቡ ስለተገደሉ እንኳን ደስ ያላችሁ፣የዛሬውን ቀን
የምናሳልፈው በትምህርት ሳይሆን በሆታና በጭፈራ ነው'
በማለት እኔን እያስመሩ በኋላ ተማሪዎቹ እየተከተሉ ወንድሜ
አስከሬን ዘንድ ደረስን። አስከሬኑን ሳልረግጥ በሁለት እግሬ
መካከል አድርጌ ሳልፍ አቶ እንድርያስ ቡታ ማጅራቴን በመያዝ
በትዕዛዝ አጠራር፣ 'ሰለሞን' በማለት 'ሬሳ እኮ የሚረገጠው
እንዲህ ነው' በማለት በወንድሜ አስከሬን ላይ ቆመበት። ከዚያ
ሳልወድ በግድ የወንድሜን አስከሬን ሆዱ ላይ ረግጬ
አልፊያለሁ።
በሁለት ረድፍ የሚሄዱ የትምህርት ቤቱ ሁለት ሽፍት ቁጥራቸው
በግምት 2,200(የሚደርስ) ተማሪዎች ለገበያ የተገኘው ሰው
ሁሉ አስከሬኑን እንዲረግጥ ተደርጓል።...
"...ገብሬ ሙሄ የተባለው የጉብሬ ት/ቤት የ8ኛ ክፍል ተማሪ
የፈጥኝ ታስሮ ከበሬ ጭራ ጋር አስረውት በሬው እየጎተተው ገ/
ጊዮርጊስ ስ�ርአት፣ገረመው እንዳለ፣ ሎባ ኸሊልና ሌሎች
በርካታ ሰዎች በመሆን እየደበደቡት ራሱ ተፈነካክቶ ፈርስ በአፉ
እየወጣ(ስርዝ-ደራሲው) ሲወስዱት አይቻለሁ' ይላል ይህ
ወጣት"...ክፍሉ ታደስ ኢትዮጵያ ሆይ ቅፅ 1 ከገፅ 65 እስከ
66) ይቺ ትንሿ ናት ታዲያ

Translate

About Me