Search This Blog

Saturday 16 July 2016

ደርግ እንዴት ሊናፍቀን ይችላል? እንዴትም!!
(የመንግስቱን ፎቶ እየለጠፋችሁ ለምታዝጉን ሰዎች ይሁን)
@@@@@@@@@@@@
"....ጠዋት ሚያዝያ 19ቀን 1970 ዓ.ም
በግምት ከንጋቱ 12
ሰዓት ቤታችን ሆነን የተኩስ ድምፅ ሰማን።...በዚያኑ ቀን ወደ
ትምህርት ቤት ስሄድ ወንድሜ ወልደ አብ ደንቡ ተገድሎ
አሥከሬኑ ከቀበሌው ፅ/ቤት ፊትለፊት ካለ አስፓልት መንገድ
ላይ ተጥሎ አይቼ ዝም ብየ በማለፍ ትምህርት ቤት ገባሁ።.....
((ወደ አስከሬኑ(ተጨምቆ)) ከመሄዳችን በፊት በስልፉ ላይ አቶ
ታደሰ መንገሻ፣ ገ/ጊዮርጊስ ስራቱና እንድርያስ ቡታ ሆነው
ስሜን ጠርተው በማውጣት በታጣቂዎች ካስያዙን በኋላ
ለተማሪዎቹ 'የሰባት ቤት ጉራጌ ቀንደኛ መሪ የሆኑት
እነወልደአብ ደንቡ ስለተገደሉ እንኳን ደስ ያላችሁ፣የዛሬውን ቀን
የምናሳልፈው በትምህርት ሳይሆን በሆታና በጭፈራ ነው'
በማለት እኔን እያስመሩ በኋላ ተማሪዎቹ እየተከተሉ ወንድሜ
አስከሬን ዘንድ ደረስን። አስከሬኑን ሳልረግጥ በሁለት እግሬ
መካከል አድርጌ ሳልፍ አቶ እንድርያስ ቡታ ማጅራቴን በመያዝ
በትዕዛዝ አጠራር፣ 'ሰለሞን' በማለት 'ሬሳ እኮ የሚረገጠው
እንዲህ ነው' በማለት በወንድሜ አስከሬን ላይ ቆመበት። ከዚያ
ሳልወድ በግድ የወንድሜን አስከሬን ሆዱ ላይ ረግጬ
አልፊያለሁ።
በሁለት ረድፍ የሚሄዱ የትምህርት ቤቱ ሁለት ሽፍት ቁጥራቸው
በግምት 2,200(የሚደርስ) ተማሪዎች ለገበያ የተገኘው ሰው
ሁሉ አስከሬኑን እንዲረግጥ ተደርጓል።...
"...ገብሬ ሙሄ የተባለው የጉብሬ ት/ቤት የ8ኛ ክፍል ተማሪ
የፈጥኝ ታስሮ ከበሬ ጭራ ጋር አስረውት በሬው እየጎተተው ገ/
ጊዮርጊስ ስ�ርአት፣ገረመው እንዳለ፣ ሎባ ኸሊልና ሌሎች
በርካታ ሰዎች በመሆን እየደበደቡት ራሱ ተፈነካክቶ ፈርስ በአፉ
እየወጣ(ስርዝ-ደራሲው) ሲወስዱት አይቻለሁ' ይላል ይህ
ወጣት"...ክፍሉ ታደስ ኢትዮጵያ ሆይ ቅፅ 1 ከገፅ 65 እስከ
66) ይቺ ትንሿ ናት ታዲያ

No comments:

Post a Comment

Translate

About Me