Search This Blog

Saturday 16 July 2016

Maalan jira
መኪና ስላለህ በእግርህ ወይ በታክሲ አትሄድም አይደል? ትልቅ
ቪላ ቤትህ ውስጥ ብፌ ተዘጋጅቶ ስለምትመገብ አነስ ያሉ
ሆቴሎች እና ምግብ ቤቶች አትገባም አይደል? ግቢህ
ው�ስጥ እሳት አያይዘህ በግ አርደህ በውስኪ ስለምታወራርድ
አነስተኛ መጠጥ ቤቶች እና ጭፈራ ቤቶች አትገባም ይሆናል።
በቃ ተበድለሃል። የሰዎች ፍቅር ተነፍጎሃል። በዚህ ቅንጡ ኑሮህ
ውስጥ በመደበቅህ ወይም ታች ያለ ኑሮ በመናቅህ የሚገርም
ፍቅር አጥተሃል። የማያውቅህ ሰው ፍቅር። የማያውቅህ ሰው
ግፊያ እና ይቅርታ። በዚያውም ትውውቅ። በዚያው ጥልቅ
ወዳጅነት።ቢዚያው ችግሮቻቸውን ማወቅ እና ማየት።እስኪ
በሞቴ ከላይ የነገርኩህን ለአንድ ሳምንት እንኳ አድርገው። ቆይ
እንዲያውም እኔ አነስተኛ ጭፈራ ቤት ይዤህ ልግባማ። ደብረ ብረሃን ነው።ቤቷ
አነስተኛ ናት። ጥቅጥቅ ብላ ሞልታለች። ጥግ ጥግ ባንኮኒ ላይ
ተደግፈው ከሚጠጡት ውጪ ሁሉም ጨርቃቸውን ጥለው
ይጨፍራሉ። ይተቃቀፋሉ። አንዱ ጆሮውን አጎንብሶ ወደ ሌላኛው
ሰው አፍ አስጠግቶ ወሬ ይቀበልና ድጋሚ ያኛው ደግሞ
ጆሮውን ለዚያኛው ሰው ያቀብላል። እልፍ ብሎ የቢራ ጠርሙስ
ይጋጫል። ቺርስስስ! ይቺን አጭር ግዜ በደስታ ለማሳለፍ፤
ያለብንን የህይወት ውጣ ውረድ ለመርሳት፤ ከቤት፣ከሚስት
ወይም ከሌላ ሰው ለመሸሽ፤ ብስቶን ለመተንፈስ ወይ
ለመርሳት፤ብቻ ይጠጣለታል። ጥጉ በሙሉ በመያዙ የቢራየን
አንገት በእጄ አቅፌ ወደ መሃል ገባሁ። ካለ ውዝዋዜ መቆምና
መጠጣት የለም የተባለ ይመስል ቤቷ ወዲያ ወዲህ ትላጋለች።
አንዱ ሙዚቃ አልቆ ሌላው ሙዚቃ ሲገባ የጭፈራ ስልቱ
ተቀይሮ ሌላ ድባብ ይፈጠራል። እዚህ በየ ሰከንዱ ሙዚቃ
ብትቀይር የሚከስስህ የለም። የጭፈራ ስልት ይቀየራል እንጂ።
የሃጫሉ ሁንዴሳ "ማለንጅራ*" ተከፈተ። ያቺ ቤት ተርገበገበች።
ጨፋሪው ትከሻውን እያወዛወዘ መሬቱን በእግሩ እየመታ ቤቷ
እሪሪ ልትል ደረሰች። የዚያ ሁሉ ሰው ትንፋሽ ከመስተዋቱ ላይ
ጤዛ ሰርቶ "ጠብ" ይላል። ሰው ፊቱ ላይ እንደ ጎርፍ
የሚንቆረቆረውን ላብ በጃኬቱ እየጠረገ ያብዳል። በእጄ
የያዝኩትን ቢራ ስጎነጨው ከወትሮው ለየት ብሎ ጣፈጠኝ። ግን
ሞቋል። ያም ቢሆን ይጣፍጣል። ሙዚቃው ሲያልቅ አጣገቤ
ላብበላብ ሆኖ ሲጨፍር የነበረ ወጣት ወደ ጆሮየ ጠጋ ብሎ ደስ
በሚል ቅላፄ
"በናትህ ሙዚቃውን አስደግምልኝ። እኔ ኦሮሞ ነኝ።ዘፈኑን
እወደዋለሁ" አለኝ። ሄጄ ለሙዚቃ አጫዋቹ ሙዚቃውን
እንዲደግምልን ነገርኩት። ሃጫሉ ተደገመ። ልጁ በደስታ
ሰከረ።ድንገት ከአጠገቤ ተሰወረ። ዞር ዞር ስል የለም። ወዲያው
ከጀርባየ ያልተከፈተ ቢራ ታቅፎ መጣ። ጠርሙሳችንን አጋጨን።
አይደክመውም። ሙዚቃው እስከሚያልቅ ጨፈረ። ሌላ ሙዚቃ
ቀጠለ። ጎጃምኛ። ቤቷ አትቆምም። በማንኛውም ሙዚቃ
ይጨፈራል፤ ይጠጣል። በተጀመረው ሙዚቃ እየጨፈረ ያ ልጅ
በድጋሚ "በናትህ የሃጫሉን አስደግምልኝ" አለኝ።
አለመነታሁም። አስደገምኩለት። ለምን ተደገመ አይባልም። ብቻ
ያስጨፍር እንጂ እኔ ራሱ ተነስቼ ብዘፍን የሚቃወም የሚኖር
አይመስለኝም። ምክንያቱም ይህ ጭፈራ ቤት ነውና። ሙዚቃው
ሲጀምር ልጁ የጭፈራ እብደቱ ተነሳበት። እሱ ብቻ አይደለም።
ጭፈራ ቤቱ ውስጥ ያሉ ሁሉ አቧራ የለም እንጂ አቧራውን
አጨሱት። ሙዚቃው ሲያልቅ ወደ ባንኮኒው እየጎተተ ይዞኝ ሄዶ
ፍላጎቴን እንኳ ሳይጠይቀኝ "10 ቢራ ስጠው" ብሎ የ10 ቢራ
ከፍሎ በትከሻው ሰላም ብሎኝ ተጠባብቆ የሚጨፍረውን ሰው
በእጁ እየፈለፈለ ጥሎኝ ወጣ። ምክንያቱም ውስጡን
የሚያይበት ወይም ብሶቱን የሚረዳበትን ነገር አግዠዋለሁና
መሰለኝ!! እናማ ከዚህ በፊት በአይን እንኳ አላውቀውም። እናም
አልኩ። መኪናም ይኑርህ በእግርህም በታክሲም ተንቀሳቀስ።
የፈለገ ድሃ ባትወድ ግዴለም ይሄ ማህበረሰብ የሚውልበት ቦታ
ዋል። ክብሬ ምንትስ አትበል። በስራ ሰዓትህ የፈለገ ትልልቅ
የሃገር ጉዳይ ስታስፈፅም ዋል። ግን በእረፍት ግዜህ ብዙሃኑ
ወደሚውልበት ሂድ። መስሪያ ቤት አብሮህ የሚውል ሰው
ፈርቶህ አልያም የራሱ ጉዳይ ብሎ ስለ አንተ ላይነግርህ
ይችላል እዚህ ግን ሳያውቅ ስላንተ የሚባለውን ሁሉ
ይነግርሃል። ራስህንም ታይበታለህ። ከፈለክም በ6ወር አንዴ
ጥንብዝ ብለህ ስከር!! ብስቶህን ተንፍሰህ ትገላገልበታለህ!!!

No comments:

Post a Comment

Translate

About Me