Search This Blog

Saturday 14 January 2017

ኮሌጅ እና ትዝታ
ትዝታ 2፦ ዘ ብሄረ ዩኒቨርሲቲ
@@@@@@@@@@@
ብሄር የሚለውን ቃል ለመጀመሪያ ጊዜ ያወኩት ዩኒቨርሲቲ ነው። ቀድሞ የማውቀው እከሌ ዘ ብሄረ ቡልጋ፣ እከሌ ዘ ብሄረ ዘጌ ምናምን በሚል ነው። ስለዚህ ብሄርን በሆነ ሰፈር ስም ነበር የማውቀው። ይህንን ነገር ፕሮፌሰር ፍቅሬ ቶሎሳ ፅፈውት በዚህ ዓመት አነበብኩት። ዩኒቨርሲቲ እየቆየሁ ስመጣ ብሄር ለሆነ ቋንቋ ተናጋሪ እንደተሰጠ ገባኝ። አማሪኛ ተናጋሪው አማራ፣ኦሮምኛ ተናጋሪው ኦሮሞ፣ ትግሪኛ ተናጋሪው ትግሬ፣ ጉራጊኛ ተናጋሪው ጉራጌ.... በሚል ተተረጎመ።እንዲህ ከሆነ ደግሞ ቋንቋ እንጂ ብሄር የሚባል ነገር የለም የሚል ድምዳሜ ውስጥ ገባሁ። በነገራችን ላይ አሁንም ቋንቋ እንጂ ብሄር የለም የሚል አስተሳሰብ ነው ያለኝ።
አማራ ልማት ማህበር፣ ኦሮሞ ልማት ማህበር፣ትግራይ ልማት ማህበር የሚሉ ማህበራት መጡና ገንዘብ አዋጡ መጣ። የአንደኛ ዓመት ተማሪዎች ወደ ግቢው ሲገቡ ተቋሙ ራሱ አቀባበል ያደርጋል። ከዚያ ዝቅ ሲል ደግሞ በትምህርት ክፍል ተማሪዎች "እንኳን ደህና መጣችሁ" ይባላሉ። ቆይቶ አስቀያሚው አቀባበል መጣ የአማራ ተወላጆች የኦሮሞ ተወላጆች የትግራይ ተወላጆ አቀባበል እየተባለ ከግቢው ውጪ ፕሮግራሞች መዘጋጀት ጀመሩ። ፑል ቤት እውላታለሁ እንጂ እንዲህ ያሉ ፕሮግራሞች ላይ መገኘት አይመቸኝም። ከቡዘና መልስ ያን ግዜ ብሄር የሚባለው የቋንቋ ክፍፍል ፍንትው አለልኝ። ትምህርት ቤት አይደል!!
የእኛ ክፍል በስልጣንም በነጥብ ሰቀላም ከፍተኛ ፊክክር የነበረበት ክፍል ነው። በየአመቱ መፈንቅለ ነጥብ ተደርጓል። ወዳጄ ምስክር አንደኛ አመት ላይ ሰቀለች።ሁለተኛ አመት ላይ ወዳጄ ያየሰው ካለምንም ደም መፍሰስ የተሳካ መፈንቅለ ነጥብ አድርጎ ሰቀለ። አንደኛ አመት እስጢፈኖስ የሚል ፊልም ሲሰሩ ስለነበር ለዚያ ነው የተዘረርኩት እያለ አሁን ድረስ ሲቆጭ ሰምቻለሁ። ያየሰው ግዕዝ የማይችል ነገር ግን እኔን ግዕዝ ያስኮረጀ ብቸኛ ሰው ነው።ካገኛችሁት ና "C"ህን ውሰድ በሉልኝ።ሶስተኛ ዓመት ላይ እኛም ፊልም ጀምረን የምማርበት ክፍል ሁላ ጠፍቶብኝ ነበር። ተመርቀን ከወጣን በኋላ ይህንን ፊልም ያየች የ8 ዓመት ልጅ ኮብል ስቶን ስጠርብ አይታ "ቱ ሞት ይሻላል። ፊልም እየሰራህ ድንጋይ ትጠርባለህ?" ብላኛለች። ከዚያ ወዲህ የካሜራ ፎብያ ተጠናወተኝ።
ዩኒቨርስቲያችን አሉኝ የሚላቸው 3 በጣም ዝነኛ ሰካራሞች ነበሩ። አንደኛው አንድ ቀን እኔ ፑል ቤት አምሽቼ እሱ ደግሞ ጠላ ቤት አምሽቶ ወደ ግቢ ሲገባ ተገናኘን። ግቢው ውስጥ ግንባታ ይካሄድ ስለነበር ትልቅ ጉድጓድ አለ። የተወሰነ ውሃም አለበት። ወደ ግቢ የሚያስገባውን ዋናውን መንገድ ትቼ ወጣ አልኩና ጉድጓዱን ዘልየ ተሻገርኩ። ልጁ በጣም ከመስከሩ የተነሳ (እፅም የወሰደ ይመስለኛል) እኔ ተንደርድሬ ዘልየ ስሻገር ከትትት ብሎ ሳቀብኝ እና
"ከዚያ ድረስ የተንደረደርክው ይቺን ለመዝለል ነው?" አለኝ። አሳሳቁ በጣም ያበሳጫል። እጁን ሆዱ ውስጥ ወሽቆ አጎንብሶ ነው የሚስቀው።ክክክክ..
"እኔማ ራመድ ብየ ነው የምሻገራት" ብሎ አንደኛው እግሩን አንስቶ ውሃው ውስጥ ቸርፏ አለበት። በውሃ እና ጭቃ በስብሶ እየተንዘረዘረ ወደ መኝታ ክፍሉ ገባ። ጠዋት ሱሪውን ሲያጥብ አገኘሁት።
አንደኛው ጓደኛችን ዶርሙ ውስጥ የሄድፎን ብጥስጣሽ ቀጣጥሎ ከመኝታው ዘንግ ጋር አገናኝቶ ሲደንስ ተገኝቶ "ፈታ" ተብሎ ተወራበት። ያንን ለምን እንዳደረገ እስከ አሁን ባይገባኝም ተመርቆ በመንግስት መስሪያ ቤት ኋላፊ ሆኗል። በነገራችን ላይ ሰቃይ የሚባል ተማሪ እና መንግስት ፈፅሞ እንዲታማበት የማይፈልግ ልጅ ነው። ዶርም ውስጥ የፖለቲካዊ ጉዳዮች ተነስተው ክርክር ከተደረገ እና ከተሸነፈ "እናታችሁን ልቀፍላችሁ" ብሎ ተነስቶ ይወጣል።
3ኛ አመት ተማሪ እያለን የውሃ ቀንን ድምቅ ባለ ሁኔታ አክብረን ማታ ረብሻ ተነሳ። ረብሻው የተነሳው ሃሙስ ቀን ስጋ ሳይቀርብ ቀርቶ ለእሁድ በመቀየሩ እና እሁድ እለትም ሳይቀርብ በመቅረቱ ነው። በጣም የሚያበሳጨው ግን ብጥብጡን ያስነሳው የውሃ ቀን መከበሩ ነው ተብሎ ተሳበበ። ጉዳዩ ደግሞ ቀጥታ ወደ እኛ ጋር ይመጣል- ወደ ጂሲ ኮሚቴው። በራሳቸው ጥፋት እንደሆነ ተማመንን። ማታ የመጀመሪያዎቹ አምስት ልጆች እስር ቤት ገባን።
እኔ እራት ለመብላት ከዶርም ወደ ውጭ ስወጣ ኮሊደር ላይ ተይዤ (ከነ ችጋሬ)
ከድር ከሽንት ቤት ሲወጣ ተይዞ
ባላቶሊ ከውጭ ወደ ግቢ ሲገባ በእንግሊዝኛ መልስ መልሶ
አንዱ ጩቤ ኪሱ ተገኝቶበት
አንዱ ተማሪ ያልሆነ የግቢ ሳር አጫጅ ግቢ ውስጥ ይዘውት (ምስኪን)
እኛ ከዚያ በኋላ የሆነውን ማየት አልቻልንም። እኛ ያለጥፋታቸው ነው የታሰሩት ተብለን ስንለቀቅ ባለጩቤው ቀረ። ስንወጣ ጓደኞቼ ወሬ አስወርተውብኝ ሲናፈስ አገኘሁ። አዲስ ሲገረፍ "ታንክ ዶርም ደብቄያለሁ" ብሎ አለ ብለው ተወራብኝ። ያሳለፍንው ግዜ እንዴት ደስስስ ይላል መሰላችሁ!! ...በናታችሁ ወደ ዩኒቨርሲቲ መልሱን
ኮሌጅ እና ትዝታ
ትዝታ 2፦ ዘ ብሄረ ዩኒቨርሲቲ

@@@@@@@@@@@
ብሄር የሚለውን ቃል ለመጀመሪያ ጊዜ ያወኩት ዩኒቨርሲቲ ነው። ቀድሞ የማውቀው እከሌ ዘ ብሄረ ቡልጋ፣ እከሌ ዘ ብሄረ ዘጌ ምናምን በሚል ነው። ስለዚህ ብሄርን በሆነ ሰፈር ስም ነበር የማውቀው። ይህንን ነገር ፕሮፌሰር ፍቅሬ ቶሎሳ ፅፈውት በዚህ ዓመት አነበብኩት። ዩኒቨርሲቲ እየቆየሁ ስመጣ ብሄር ለሆነ ቋንቋ ተናጋሪ እንደተሰጠ ገባኝ። አማሪኛ ተናጋሪው አማራ፣ኦሮምኛ ተናጋሪው ኦሮሞ፣ ትግሪኛ ተናጋሪው ትግሬ፣ ጉራጊኛ ተናጋሪው ጉራጌ.... በሚል ተተረጎመ።እንዲህ ከሆነ ደግሞ ቋንቋ እንጂ ብሄር የሚባል ነገር የለም የሚል ድምዳሜ ውስጥ ገባሁ። በነገራችን ላይ አሁንም ቋንቋ እንጂ ብሄር የለም የሚል አስተሳሰብ ነው ያለኝ።
አማራ ልማት ማህበር፣ ኦሮሞ ልማት ማህበር፣ትግራይ ልማት ማህበር የሚሉ ማህበራት መጡና ገንዘብ አዋጡ መጣ። የአንደኛ ዓመት ተማሪዎች ወደ ግቢው ሲገቡ ተቋሙ ራሱ አቀባበል ያደርጋል። ከዚያ ዝቅ ሲል ደግሞ በትምህርት ክፍል ተማሪዎች "እንኳን ደህና መጣችሁ" ይባላሉ። ቆይቶ አስቀያሚው አቀባበል መጣ የአማራ ተወላጆች የኦሮሞ ተወላጆች የትግራይ ተወላጆ አቀባበል እየተባለ ከግቢው ውጪ ፕሮግራሞች መዘጋጀት ጀመሩ። ፑል ቤት እውላታለሁ እንጂ እንዲህ ያሉ ፕሮግራሞች ላይ መገኘት አይመቸኝም። ከቡዘና መልስ ያን ግዜ ብሄር የሚባለው የቋንቋ ክፍፍል ፍንትው አለልኝ። ትምህርት ቤት አይደል!!
የእኛ ክፍል በስልጣንም በነጥብ ሰቀላም ከፍተኛ ፊክክር የነበረበት ክፍል ነው። በየአመቱ መፈንቅለ ነጥብ ተደርጓል። ወዳጄ ምስክር አንደኛ አመት ላይ ሰቀለች።ሁለተኛ አመት ላይ ወዳጄ ያየሰው ካለምንም ደም መፍሰስ የተሳካ መፈንቅለ ነጥብ አድርጎ ሰቀለ። አንደኛ አመት እስጢፈኖስ የሚል ፊልም ሲሰሩ ስለነበር ለዚያ ነው የተዘረርኩት እያለ አሁን ድረስ ሲቆጭ ሰምቻለሁ። ያየሰው ግዕዝ የማይችል ነገር ግን እኔን ግዕዝ ያስኮረጀ ብቸኛ ሰው ነው።ካገኛችሁት ና "C"ህን ውሰድ በሉልኝ።ሶስተኛ ዓመት ላይ እኛም ፊልም ጀምረን የምማርበት ክፍል ሁላ ጠፍቶብኝ ነበር። ተመርቀን ከወጣን በኋላ ይህንን ፊልም ያየች የ8 ዓመት ልጅ ኮብል ስቶን ስጠርብ አይታ "ቱ ሞት ይሻላል። ፊልም እየሰራህ ድንጋይ ትጠርባለህ?" ብላኛለች። ከዚያ ወዲህ የካሜራ ፎብያ ተጠናወተኝ።
ዩኒቨርስቲያችን አሉኝ የሚላቸው 3 በጣም ዝነኛ ሰካራሞች ነበሩ። አንደኛው አንድ ቀን እኔ ፑል ቤት አምሽቼ እሱ ደግሞ ጠላ ቤት አምሽቶ ወደ ግቢ ሲገባ ተገናኘን። ግቢው ውስጥ ግንባታ ይካሄድ ስለነበር ትልቅ ጉድጓድ አለ። የተወሰነ ውሃም አለበት። ወደ ግቢ የሚያስገባውን ዋናውን መንገድ ትቼ ወጣ አልኩና ጉድጓዱን ዘልየ ተሻገርኩ። ልጁ በጣም ከመስከሩ የተነሳ (እፅም የወሰደ ይመስለኛል) እኔ ተንደርድሬ ዘልየ ስሻገር ከትትት ብሎ ሳቀብኝ እና
"ከዚያ ድረስ የተንደረደርክው ይቺን ለመዝለል ነው?" አለኝ። አሳሳቁ በጣም ያበሳጫል። እጁን ሆዱ ውስጥ ወሽቆ አጎንብሶ ነው የሚስቀው።ክክክክ..
"እኔማ ራመድ ብየ ነው የምሻገራት" ብሎ አንደኛው እግሩን አንስቶ ውሃው ውስጥ ቸርፏ አለበት። በውሃ እና ጭቃ በስብሶ እየተንዘረዘረ ወደ መኝታ ክፍሉ ገባ። ጠዋት ሱሪውን ሲያጥብ አገኘሁት።
አንደኛው ጓደኛችን ዶርሙ ውስጥ የሄድፎን ብጥስጣሽ ቀጣጥሎ ከመኝታው ዘንግ ጋር አገናኝቶ ሲደንስ ተገኝቶ "ፈታ" ተብሎ ተወራበት። ያንን ለምን እንዳደረገ እስከ አሁን ባይገባኝም ተመርቆ በመንግስት መስሪያ ቤት ኋላፊ ሆኗል። በነገራችን ላይ ሰቃይ የሚባል ተማሪ እና መንግስት ፈፅሞ እንዲታማበት የማይፈልግ ልጅ ነው። ዶርም ውስጥ የፖለቲካዊ ጉዳዮች ተነስተው ክርክር ከተደረገ እና ከተሸነፈ "እናታችሁን ልቀፍላችሁ" ብሎ ተነስቶ ይወጣል።
3ኛ አመት ተማሪ እያለን የውሃ ቀንን ድምቅ ባለ ሁኔታ አክብረን ማታ ረብሻ ተነሳ። ረብሻው የተነሳው ሃሙስ ቀን ስጋ ሳይቀርብ ቀርቶ ለእሁድ በመቀየሩ እና እሁድ እለትም ሳይቀርብ በመቅረቱ ነው። በጣም የሚያበሳጨው ግን ብጥብጡን ያስነሳው የውሃ ቀን መከበሩ ነው ተብሎ ተሳበበ። ጉዳዩ ደግሞ ቀጥታ ወደ እኛ ጋር ይመጣል- ወደ ጂሲ ኮሚቴው። በራሳቸው ጥፋት እንደሆነ ተማመንን። ማታ የመጀመሪያዎቹ አምስት ልጆች እስር ቤት ገባን።
እኔ እራት ለመብላት ከዶርም ወደ ውጭ ስወጣ ኮሊደር ላይ ተይዤ (ከነ ችጋሬ)
ከድር ከሽንት ቤት ሲወጣ ተይዞ
ባላቶሊ ከውጭ ወደ ግቢ ሲገባ በእንግሊዝኛ መልስ መልሶ
አንዱ ጩቤ ኪሱ ተገኝቶበት
አንዱ ተማሪ ያልሆነ የግቢ ሳር አጫጅ ግቢ ውስጥ ይዘውት (ምስኪን)
እኛ ከዚያ በኋላ የሆነውን ማየት አልቻልንም። እኛ ያለጥፋታቸው ነው የታሰሩት ተብለን ስንለቀቅ ባለጩቤው ቀረ። ስንወጣ ጓደኞቼ ወሬ አስወርተውብኝ ሲናፈስ አገኘሁ። አዲስ ሲገረፍ "ታንክ ዶርም ደብቄያለሁ" ብሎ አለ ብለው ተወራብኝ። ያሳለፍንው ግዜ እንዴት ደስስስ ይላል መሰላችሁ!! ...በናታችሁ ወደ ዩኒቨርሲቲ መልሱን
የኮሌጅ ትዝታ
ግልባጭ ለደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች

((((((((((((((((((((((((((((((((())))))))))))))))))))))))))))
ትዝታ 1, ኮሌጅ እና ፖለቲካ
@@@@@@@@@
"የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች" እንደተባልን የመጀመሪያው ምርጫ ትምህርት ክፍል መረጣ ነው። የእኛ የመጀመሪያ ምርጫ የነበረው ግን "ዱርየ እንሁን ወይስ አንሁን" የሚለው ነው። በአብላጫ ድምፅ ዱርየ እንድንሆን ተወሰነ። ነብር የገደልን ይመስል ፀጉር አሳደግን፣እንደ ጀግና ጆሮ ጉትቻ አደረጉ (እኔ ጆሮ መበሳት ስለማይመቸኝ አልተበሳሁም) ሱሪያችንን ዝቅ አደረግን፤ የግቢውን አቧራ ለመከላከል በሚል ሱሪያችንን ከታች አጥፈን በብር ማሰሪያ ላስቲክ አሠርን። ቆይቶ ላስቲኩ አልበረክት ቢለን በኮንዶም ጫፍ ማሰር ጀመርን። ከተማ ገብተን በ2 ብር 8 ሙዝ 4ቱን በብር 4ቱን አጭበርብረን ገዝተን መብላት ሙዳችን ሆነ። ዱርየዎች ሆንን። ፑል ቤት 1ሰው ቁማር ለመብላት 3 ሰው አሰለፍን። የግቢ በር እየተዘጋብን ከጅብ ጋር እየታገልን በጫካ መግባት ጀመርን። (የእኛ ግቢ ከአንድ በኩል ሙሉ ለሙሉ ጫካ ስለነበር አጥር አልነበረውም። ስለዚህ ፈሪ ካልሆንክ በቀር በር ተዘግቶብህ ውጭ አታድርም) እንዲህ እንዲህ እያልን የመጀመሪያው መንፈቅ አመት ተጠናቀቀ። የዱርየው ቡድን አብዛኛው ሰው በውጤት ሰቃይ ሆኖ ተገኘ።'እነዚህ ልጆች ሰው እያዘናጉ' ተባለ። እኛ ክፍል ደንግጦ ነው መሰለኝ የሰቀለብን Miskir Agegnehu ነው። መጨረሻ ላይ ግን Yayesew Shimelis ጠቀለለን። ቆይቶ እኔ እና ምስክር ከአንደኛው መምህር ጋር ተጣላን። ምስክርን ሽማግሌው በእርግጫ ሲመቱት እኔ ፀጉርህን ሳትቆረጥ እንዳትገባ ተባልኩ። የመምህሩ እግር አነሳስ አሁንም አይኔ ላይ አለ። ከክፍል መቅረት የማይታሰብ ስለነበር እኔ በማግስቱ ፀጉሬን ተቆርጨ ገባሁ። "ቲቸር ይሄው ተቆረጨ መጣሁ" ብላቸው "እኔ እኮ ትንሽ አጠር አድርገው ነበር እንጂ እንዲህ ተቆረጠው አላልኩም" ብለው አስፈቱኝ (አናደዱኝ)። ነፍስ ይማር ድሬር!! በአመቱ መጨረሻ መምህር ስንገመግም መምህሩ "በእርግጫ ተማሪ ይማታሉ" ሲባሉ "እኔ አላስታውስም" አሉ። የአራዳ ልጅ!! እንዲህ እንዲህ እያለ የእኛ ክፍል አንገቱን ቀና ማድረግ ጀመረ። የፓለቲካው ጉዳይም ተንቀሳቀቀሰ። Z ቀንደኛ የኢህአዴግ ተቃዋሚ ነገር ግን ለብዓዴን አባል የሚመለምል ልጅ ነበር። እኔንም አንድ ግዜ "ለምን አባል አትሆንም ስትመረቅ ስራ ታገኛለህ" ብሎኝ ነበር ። "አንተ ስለምትቀጠር በጓደኝነት ታስቀጥረኛለህ" ብየው ተለያየን። ከእኛ ክፍል 2 ልጆች ብቻ አባል ያልሆንን ስንገኝ ከተለያየ ትምህርት ክፍል የተሰባሰበው የዱርየው ቡድንም እንዲሁ አንዱም አባልነት ውስጥ አልነበሩም። መጨረሻ ላይ አንዱ የክፍል ጓደኛየ "ምን ቸገረህ ዝም ብለህ አባል ሁን" ብሎኝ ስብሰባ እንድገኝ አደረገኝ። ዩኒቨርሲቲው ግቢ ውስጥ የፖለቲካ ስብሰባ ማድረግ ስለማይቻል ጫካ ውስጥ ለመጀመሪያ ግዜ ተሰበሰብኩ። ግምገማ ተጀመረ።
"አንተ በግ ተራ መቆም ታበዛለህ፣ እገሌ ከእንትና ጋር ተጣልተዋል እና የተጣሉት ደግሞ በዚህ ምክንያት ነው፤ አንተ መንገድ ላይ ሰላም አትለንም" ምናምን የሚሉ የግምገማ ሃሳቦች መምጣት ሲጀምሩ ስብሰባውን አቋርጬ በዚያው ጫካ ገባሁ።(ጫካ ስል ደግሞ ሌላ እንዳይመሥላችሁ። ከጫካው ውስጥ ኳስ የምንጫወትበት ሜዳ ስላለ ነው) ከዚያ ወዲህ የማንኛውም የፖለቲካ ድርጅት አባል ሳልሆን እስከ አሁን አለሁ። 2ኛ እና 3ኛ ዓመት ላይ ክበባት ውስጥ መሳተፍ ጀመርኩ። ቆይቶ የመዝናኛና ስነ-ፅሁፍ ክበብ ምክትል ፕሬዝዳንትነት ስልጣን ተሰጠኝ።( ሃሃ ም/ፕሬዝዳንት!!) የግቢው ስልጣን የሃይል ሚዛን ወደ እኛ ክፍል አመራ። የተማሪዎች ህብረት ምክትል ፕሬዝዳንት፣የጂሲ ኮሚቴ ምክትል ፕሬዝዳንት፣የፀረ ኤድስ ክበብ ምክትል ፕሬዝዳንት፣የመዝናኛና ስነ-ፅሁፍ ክበብ ምክትል ፕሬዝዳንት፣ የጂሲ ኮሚቴ መዝናኛና ስነፅሁፍ ክፍል ተጠሪ የሚባሉት ስልጣኖች ተጠቅልለው እኛ ክፍል መጡ።ተሿሚዎች Gtnet Asrat Yayesew Shimelis Gashaw Eshetu አዲስ መኮንን :: እኔ በመዝናኛና ስነ - ፅሁፍ በምክትል ፕሬዝዳንትነት ማዕረግ የጂሲ ኮሚቴውን የመዝናኛ ክፍል ተጠሪነት ደርቤ ያዝኩ። ስልጣን ሲመጣ እንዲህ ነው!! ይሄ የሆነው ግን ዱርየነቴን ከተውኩ በኋላ ነው።በእነዚህ አይነት የስልጣን ክፍፍል የሃይል ሚዛኑ ከአንድ ክፍል ወጥቶ ወደ ሸዋ አደላ ተብሎም ብዙ ታማን። የፖለቲካው የሃይል ሚዛን ደግሞ ወደ ጎጃም እና ጎንደር አምርቷል ተባለ። የብአዴንን አባልነት አብዛኛውን ስልጣን እነሱ ይዘውታል ተብሎ ቅሬታ የቀረበበት የምስራቅ ጎጃም ዞን የብአዴን ፅህፈት ቤት ኋላፊ መሰለኝ
"የሸዋ ሰው አትንኩኝ አልነካችሁም ፤ አትድረሱብኝ አልደርስባችሁም ነው። እና እኛ ምን እናድርጋችሁ" አለን ብለው ሢያስቁን ነበር።
እኔ በስልጣን ዘመኔ (ከ2003 -2004) የበደልኩት ወይም የጨቆንኩት ሰው ባይኖርም የስነ ፅሁፍ ምሽት ስናዘጋጅ ተማሪ እየበዛ በመምጣቱ አንድ ቀን አዳራሽ ሞልቶብን በር እንዲዘጋ እና ተማሪ እንዳይገባ አዝዤ ነበር። ያን ግዜ "ተማሪዎችን ስነ-ፅሁፍ ምሽት ላይ ገንዘብ እያስከፈለ አስገባ" ተብሎ ተወራብኝ። የስለላ መረቤን ዘርግቼ ጉዳዩን ሳጣራ በር ላይ የነበሩ ልጆች የተማሪውን መብዛት አይተው የተወሰኑ ተማሪዎችን እያስከፈሉ እንዳስገቧቸው ደረስኩበት። ልጆቹን አድሳለሁ ስል እኔም ሳላድሳቸው እነሱም ለእድሳት ሳይበቁ ተመርቀን ወጣን። ይብላኝ ለቀጠራቸው ተቋም!!
በስልጣን ዘመኔ የሚቆጨኝ ግን የምረቃ መፅሄታችን ላይ የወጣው የስነ-ፅሁፍ ስራ ነው። በጣም ጥሩ ጥሩ የስነ-ፅሁፍ ስራዎችን ገምግመን ካፀደቅን በኋላ ሁለቱን ልጆች ለአርትኦት ስራ አዲስ አበባ ልከናቸው አንደኛው ለፍቅረኛው የፃፈላትን ደብዳቤ የሚመስል ግጥም አትሞበት መጣ።
በስተመጨረሻ ከእኛ ክፍል መንግስትን ክፉኛ ይቃወም የነበረ ልጅ ሃገሩ ገብቶ የወጣት ሊግ ሰብሳቢ ሆኖ አግኚቼው "ምነው?" ብለው
"አብዮታዊ ዲሞክራሲ ተጠምቄያለሁ"ብሎ አለኝ። ምስኪን Z ደግሞ ለብዓዴን አባል ስትመለምል ከርማ መጨረሻ ላይ ሰክሮ ነው አሉ "የወያኔን ዲግሪ ማየት አልፈልግም" ብሎ ግዜያዊ የዲግሪ ወረቀቱን መንገድ ላይ እንደቀደደው ሰምቻለሁ)።
ክንፍፍፍፍ ያለ ፍቅር ያየዘኝም ያን ግዜ ነበር።
"ያሳለፍነው ግዜ ደስታን ያየንበት
ተመልሶ ቢገኝ አሁን ምን አለበት" አለ ጥልሽ!!
የሩስያ እና የአሜሪካ ፍጥጫ
@@@@@@@@@@@
ምንም እንኳ የእነዚህ የሁለት ጡንቻማ ሃገራት መማዘዝ ቆይቶ እኛን የመሳሰሉ ድሃ ሃገራትን ቢደፈጥጥም ፍጥጫቸው ያጓጓል። አብዛኛው አሜሪካዊ የሩስያ መግነን የሃገራቸውን ሃያልነት ይውጣል ከሚል ፍራቻ ይመስላል ቁጭት ውስጥ ናቸው። በተለይ ደግሞ ለአሜሪካ ፕሬዝዳንትነት ስትጠበቅ የነበረችው ሂላሪ ባልተጠበቀ ሁኔታ በትራምፕ መሸነፏ እና የትራምፕ ማሸነፍ ደግሞ የሩስያ እጅ ነበረበት መባሉ የሩስያን እጀ ረጅምነት እና የአሜሪካንን ዝርክርክነት ያሳየ በመሆኑ ብዙዎችን አበሳጭቷል። ሩስያ የእውነት ይህንን አድርጋ ከሆነ እውነትም ተፅዕኖ እየፈጠረች ነው። ትራምፕ እንደሚሉት እና ሲ አይ ኤ እና የአሜሪካ መገናኛ ብዙሃን በሬ ወለደ እያሉ አሜሪካንን እያሳሳቱ ነው የሚሉት ነገር ሚዛን የሚደፋ ከሆነ የሂላሪ አለመመረጥ ሄዶ ሄዶ አሜሪካ ህዝብ ላይ ያርፋል። ምክንያቱም የምርጫ ማሽኑ ካልተጠለፈ እና ትራምፕ በትክክለኛ ምርጫ ከሆነ ያሸነፉት ትራምፕ በቅስቀሳቸው ወቅት የተከተሉት አነጋጋሪ የምርጫ ቅስቀሳዎች አሜሪካውያን ልብ ውስጥ ገብተው ነበር ማለት ነው። ስለዚህ የአሜሪካ ህዝብ በሌሎች ሃገራት ሰዎች በገዛ ሃገራችን በኢኮኖሚ ተበለጥን እና ሌሎችም የሃይማኖት፣የዘር እና የመሳሰሉት ጥላቻዎች ሰርፀው ገብተውበታል ማለት ነው። ያ ደግሞ አሜሪካን ለዘመናት ገነባሁት የምትለው ዲሞክራሲን ገደል የሚከትተው ይመስላል። የሆነው ሆኖ ትራምፕ አሸንፈዋል። ለትራምፕ መመረጥ የሩስያ እጅ መኖሩን ትልቅ መተማመን አለኝ ባለው ሲ አይ ኤ መሰረት የዩ ኤስ ሲናተሮች እንደ ሃገር በሩስያ ላይ እንደ ግለሰብ ደግሞ በፑቲን ላይ ማዕቀብ መጣል አለበት እያሉ ያዙን ልቀቁን እያሉ ነው። ሩስያ በክሬምያ ጉዳይ የተጠለባት ማዕቀብ ሳይነሳ ድጋሚ ሌላ ማዕቀብ የሚጣልባት ከሆነ ካለምንም ጥርጥር መጎዳቷ አይቀርም። መዘዙ ግን ለሌሎችም ይተርፋል።2014ላይ የአውሮፓ ህብረት ማዕቀብ የጣለባት ግዜ ከዚያ አካባቢ የሚመረተውን የግብርና ምርጥ ወደ ሃገር ውስጥ አላስገባም ብላ በርካታ አምራቾችን ለኪሳራ ዳርጋለች። እንደሚታወቀው ሩስያ ከፍተኛ መጠን ያለው የግብርና ምርትን ወደ ሃገሯ ታሰገባለች። በማዕቀቡ ምክንያት አፃፋ ለመመለስ ምርት ማስገባቱን ስታቆም ሳምንት ባለሞላ ግዜ ውስጥ የምዕራቡ ዓለም አምራቾች ተንጫጩ። "እሾኽን በእሾህ" ማለት ይሄ ነው። የአሜሪካንን ጡጫ በዚህ ምድር ላይ ካለ ሩስያ የሚቋቋመው የለም። ለዚህም ነው አሜሪካ ሩስያን የሾርኒ የምትመለከታት። ለማንኛውም ስልጣናቸውን በቅርቡ ለትራምፕ የሚያስረክቡት ኦባማ ሊተላለፍ የሚችለውን ውሳኔ ይፋ ያደርጋሉ ተብሎ እየተጠበቀ ነው። ውሳኔው ምንም ይሁን ምን "አሜሪካ በምትወስነው ውሳኔ ምላሹን ወደያው ታገኘዋለች" እያሉ ነው የሩስያ ባለስልጣናት። በትራምፕ ማሸነፍ የሚብሰለሰውለው ብዙሃን መገናኛው እና ሲ አይ ኤ ጉዳዩን እያራገበ አሸናፊውን ፕሬዝዳንት አጣብቂኝ ውስጥ ሊከትቱት ነው። ከሩስያ ጋር በጋራ እንሰራለን ያሉት ትራምፕ በሩስያ ላይ ሊወሰድ የታሰበው እርምጃ የተሳሳተ እሳቤ ነው ብለው እየተከራከሩ ቢሆንም ጉዳዩ ገፍቶ ሩስያ ላይ ማዕቀብ ተጥሎ ስልጣናቸውን ከተረከቡ ማጣፊያው ሊያጥራቸው ይችላል። እውነትም በሩስያ እገዛ ከሆነ ወደ ስልጣን የመጡት ደግሞ ይቺን ባለውለታ ሃገር እንዴት አድርገው ያስቀይሟታል? አሜሪካ ከአንጀት ይሁን ከአንገት እንጃ እንጂ በእስራኤል የሰፈራ ፕሮግራም ዙሪያ ከእስራኤል ጋር እስከዚህም የመሆን አዝማሚያ እየታየባት ነው። ወዲያ ደግሞ ቻይና የታይዋይን ጉዳይ በጥንቃቄ ልታየው ይገባል እየተባለች ነው። ስልጣን የሚለቀው የኦባማ አስተዳደር ለትራምፕ ትልቅ የቤት ስራ እያዘጋጁላቸው ነው። ትረምፕ አንድ ግዜ ጡርምባውን ከነፉት "ነፍስ ይማር አሜሪካ" የሚል ድምፅ የሚያወጣ ይመስለኛል።
የሩስያ እና የአሜሪካ ፍጥጫ
@@@@@@@@@@@
ምንም እንኳ የእነዚህ የሁለት ጡንቻማ ሃገራት መማዘዝ ቆይቶ እኛን የመሳሰሉ ድሃ ሃገራትን ቢደፈጥጥም ፍጥጫቸው ያጓጓል። አብዛኛው አሜሪካዊ የሩስያ መግነን የሃገራቸውን ሃያልነት ይውጣል ከሚል ፍራቻ ይመስላል ቁጭት ውስጥ ናቸው። በተለይ ደግሞ ለአሜሪካ ፕሬዝዳንትነት ስትጠበቅ የነበረችው ሂላሪ ባልተጠበቀ ሁኔታ በትራምፕ መሸነፏ እና የትራምፕ ማሸነፍ ደግሞ የሩስያ እጅ ነበረበት መባሉ የሩስያን እጀ ረጅምነት እና የአሜሪካንን ዝርክርክነት ያሳየ በመሆኑ ብዙዎችን አበሳጭቷል። ሩስያ የእውነት ይህንን አድርጋ ከሆነ እውነትም ተፅዕኖ እየፈጠረች ነው። ትራምፕ እንደሚሉት እና ሲ አይ ኤ እና የአሜሪካ መገናኛ ብዙሃን በሬ ወለደ እያሉ አሜሪካንን እያሳሳቱ ነው የሚሉት ነገር ሚዛን የሚደፋ ከሆነ የሂላሪ አለመመረጥ ሄዶ ሄዶ አሜሪካ ህዝብ ላይ ያርፋል። ምክንያቱም የምርጫ ማሽኑ ካልተጠለፈ እና ትራምፕ በትክክለኛ ምርጫ ከሆነ ያሸነፉት ትራምፕ በቅስቀሳቸው ወቅት የተከተሉት አነጋጋሪ የምርጫ ቅስቀሳዎች አሜሪካውያን ልብ ውስጥ ገብተው ነበር ማለት ነው። ስለዚህ የአሜሪካ ህዝብ በሌሎች ሃገራት ሰዎች በገዛ ሃገራችን በኢኮኖሚ ተበለጥን እና ሌሎችም የሃይማኖት፣የዘር እና የመሳሰሉት ጥላቻዎች ሰርፀው ገብተውበታል ማለት ነው። ያ ደግሞ አሜሪካን ለዘመናት ገነባሁት የምትለው ዲሞክራሲን ገደል የሚከትተው ይመስላል። የሆነው ሆኖ ትራምፕ አሸንፈዋል። ለትራምፕ መመረጥ የሩስያ እጅ መኖሩን ትልቅ መተማመን አለኝ ባለው ሲ አይ ኤ መሰረት የዩ ኤስ ሲናተሮች እንደ ሃገር በሩስያ ላይ እንደ ግለሰብ ደግሞ በፑቲን ላይ ማዕቀብ መጣል አለበት እያሉ ያዙን ልቀቁን እያሉ ነው። ሩስያ በክሬምያ ጉዳይ የተጠለባት ማዕቀብ ሳይነሳ ድጋሚ ሌላ ማዕቀብ የሚጣልባት ከሆነ ካለምንም ጥርጥር መጎዳቷ አይቀርም። መዘዙ ግን ለሌሎችም ይተርፋል።2014ላይ የአውሮፓ ህብረት ማዕቀብ የጣለባት ግዜ ከዚያ አካባቢ የሚመረተውን የግብርና ምርጥ ወደ ሃገር ውስጥ አላስገባም ብላ በርካታ አምራቾችን ለኪሳራ ዳርጋለች። እንደሚታወቀው ሩስያ ከፍተኛ መጠን ያለው የግብርና ምርትን ወደ ሃገሯ ታሰገባለች። በማዕቀቡ ምክንያት አፃፋ ለመመለስ ምርት ማስገባቱን ስታቆም ሳምንት ባለሞላ ግዜ ውስጥ የምዕራቡ ዓለም አምራቾች ተንጫጩ። "እሾኽን በእሾህ" ማለት ይሄ ነው። የአሜሪካንን ጡጫ በዚህ ምድር ላይ ካለ ሩስያ የሚቋቋመው የለም። ለዚህም ነው አሜሪካ ሩስያን የሾርኒ የምትመለከታት። ለማንኛውም ስልጣናቸውን በቅርቡ ለትራምፕ የሚያስረክቡት ኦባማ ሊተላለፍ የሚችለውን ውሳኔ ይፋ ያደርጋሉ ተብሎ እየተጠበቀ ነው። ውሳኔው ምንም ይሁን ምን "አሜሪካ በምትወስነው ውሳኔ ምላሹን ወደያው ታገኘዋለች" እያሉ ነው የሩስያ ባለስልጣናት። በትራምፕ ማሸነፍ የሚብሰለሰውለው ብዙሃን መገናኛው እና ሲ አይ ኤ ጉዳዩን እያራገበ አሸናፊውን ፕሬዝዳንት አጣብቂኝ ውስጥ ሊከትቱት ነው። ከሩስያ ጋር በጋራ እንሰራለን ያሉት ትራምፕ በሩስያ ላይ ሊወሰድ የታሰበው እርምጃ የተሳሳተ እሳቤ ነው ብለው እየተከራከሩ ቢሆንም ጉዳዩ ገፍቶ ሩስያ ላይ ማዕቀብ ተጥሎ ስልጣናቸውን ከተረከቡ ማጣፊያው ሊያጥራቸው ይችላል። እውነትም በሩስያ እገዛ ከሆነ ወደ ስልጣን የመጡት ደግሞ ይቺን ባለውለታ ሃገር እንዴት አድርገው ያስቀይሟታል? አሜሪካ ከአንጀት ይሁን ከአንገት እንጃ እንጂ በእስራኤል የሰፈራ ፕሮግራም ዙሪያ ከእስራኤል ጋር እስከዚህም የመሆን አዝማሚያ እየታየባት ነው። ወዲያ ደግሞ ቻይና የታይዋይን ጉዳይ በጥንቃቄ ልታየው ይገባል እየተባለች ነው። ስልጣን የሚለቀው የኦባማ አስተዳደር ለትራምፕ ትልቅ የቤት ስራ እያዘጋጁላቸው ነው። ትረምፕ አንድ ግዜ ጡርምባውን ከነፉት "ነፍስ ይማር አሜሪካ" የሚል ድምፅ የሚያወጣ ይመስለኛል።
ዘረኝነት የፍቺ ምክንያት ሲሆን
@@@@@@@@@@@
እኔ የምለው በዓሉ እንዴት ነበር? ክርስቶስ ለእኛ ፍቅርን ሊያስተምር የተወለደበትን ቀን እያከበርን ነው። የዘንድሮው የልደት በዓል ከአምናው የሚለየው ዘንድሮ ጥላቻን እየዘሩ ላስቸገሩን አሁንም ፍቅርን እየተማርን የምናስተምርበት መሆኑ ነው። ልበል እንዴ? ለነገሩ አልኩ። ፍቅርን ፍቅር ከሚያውቁ ሁሉ እንማራለን። በአምሳሉ የፈጠረውን ሰው ሁሉ እንወዳለን። መውደድ ስል ምን ትዝ አለኝ መሰላችሁ ፍቅር፤ ፍቅር ስል ደግሞ ትዳር። እናላችሁ በዚህ በልደት በዓል ረፋድ ላይ ከቤት ወደ ሡቅ ስወጣ ከኋላየ አንድ ወጣት ስልክ እያወራ ይከተለኛል። በዓል እንደመሆኑ ብዙዎቹ ሱቆች ተዘግተው ጎዳናው እረጭ ብሏል። እናም ልጁ የሚያወራው በሙሉ ይሰማኛል። ከንግግሩ ከትዳር ጓደኛው ጋር እንደተለያዩ ተረዳሁ።
"እየውልህ እኔ እኮ ልጅቷን ሳልወዳት ቀርቼ አይደለም። እወዳታለሁ። እንደምትወደኝም አምናለሁ"
ይልና የዚያኛውን ስልክ ደግሞ ይሰማል። ያኛው ከሚስትህ ጋር ታረቁ እያለ እየመከረው እንደሆነ ገባኝ። በዚህ በዓል ከፍቅር እና ከትዳር መለያየት እንዴት እንደሚያስጠላ አስቡት። ግን እንዲህ የሚዋደዱ ከሆነ በምን ምክንያት ሊለያዩ ቻሉ። ልጁ ንግግሩን ቀጠለ።
"ያው የቤቱን እቃ ትቼላት ወጣሁ። ቴሌቭዥን ብትል አልጋ ሁሉንም ትቼላታለሁ እኮ!" እያለ ያወራል። ይሄ ጥል አይባልም ብየ አሰብኩ። ሰውን እየተዋደዱም ቢሆን የሚያለያየው ያ ገንዝብ የሚሉት ሰይጣን ነው ብየ እያሰብኩ እያለ
"እየውልህ እኔ ያ በረሃ የሆነን ቦታ ለእሷ ስል ነበር ተቋቁሜ የኖርኩት። አሁን ግን በቃኝ። ዘረኝነቷ አንገሸገሸኝ" ሲል ጆሮየን ማመን አቃተኝ። ከዚህ በላይ መስማት አልፈለኩም ያለ መንገዴ በቅያሱ ታጥፌ ሸሸሁት። ይሄ የዘረኝነት አባዜ ትዳር ውስጥም መግባቱ አበሳጨኝ። እግዜያብሄር በአምሳሉ የፈጠረውን ፍጡር ሰው መሆኑን ትተን ሰው ያለመሆን አባዜ ሲጠናወተን ራሴን መታኝ። አጥንት መቁጠር እዚህ ድረስ አጥንት ሰብሮ ይገባል። የማል!! ከክርስቶስ ፍቅርን እንማር። መልከም በዓል

Translate

About Me