Search This Blog

Blog Archive

Sunday 30 July 2017

ደረቅ ጭንቅላት እንጂ ደረቅ አፈር የለም

መቀሌ ነው አሉ። አንድ አውደ ጥናት ተዘጋጅቶ አንድ ፕሮፌሰር ጥናት ያቀርባሉ። ጥናቱ እፀዋት ላይ ያተኮረ ሲሆን ፕሮፌሰሩ "የግራር ዛፍ ችግኝ ችግር ስላለብን በቀላሉ ማብቀል(ማባዛት) አልቻልንም" ብለው ይናገራሉ። በአውደ ጥናቱ የተጋበዘ አንድ አርሶ አደር እጁን ያወጣና እሱ በጣም ቀላል ነው እኔ ላሳያችሁ እችላለሁ ብሎ ይናገራል። ፕሮፌሰሩ አርሶ አደሩን ምን ታውቃለህ ዝም በል አይነት ንግግር ይናገሩታል። እልህ የያዘው አርሶ አደር
"መኪና መድቡና እኔ ማሳ ድረስ ይዣችሁ ልሄድ" ብሎ ይከራከራል። ተፈቅዶለት የአውደ ጥናቱን ተሳታፊዎች ጭምር ይዘው ወደ ማሳው ያመራሉ። አርሶ አደሩ ግራሩን ያራባበትን መንገድ በተግባር እያሳየ ገልፃ አደረገላቸው። በዚህ ግዜ ፕሮፌሰሩ የሚገቡበት ይጠፋቸዋል። በዚህ የተበቃሳጨው አርሶ አደር
"ደረቅ ጭንቅላት እንጂ ደረቅ አፈር የለም" ብሎ ፕሮፌሰሩን አስገባላቸው። ይህንን የነገሩን የአውደ ጥናቱ ተሳታፊ የነበሩ ናቸው።
እነ ዶክተር ፍቀደ አዘዘ በአንድ ወቅት ለጥናት ወደ ሰሜን ሸዋ ሄደው ይመስለኛል ለጥናቱ አርሶ አደሮች ይሰበስባሉ። " እንግዲህ ለጥናቱ ሰዎች ስንመርጥ 'በራንደም ሳምፕሊንግ' ነው።ከእናንተ ውስጥ ዝም ብለን አንዳንድ ሰው እንዳገኘን እንመርጣለን" ይሏቸዋል። አንዱ አርሶ አደር
" እና በብድግ ብድግ መረጣ ነው አትሉንም ወይ?" ብለው ተናግረው ይህንን ቃል ወደ ቋንቋው አስገብተው ሲጠቀሙበት እንደነበር የፎክሎር መምህራችን ሲያስተምረን ነግሮናል። ምን ለማለት ነው ማህበረሰቡ ጋር ትልቅ እውቀት አለ። ተማርን ብለን በያዝናት ወረቀት ከምንኮፈስ ለማህበረሰቡ እውቀት እውቅና እየሰጠን መስራት ይኖርብናል። አርሶ አደሩ ጋር ተዝቆ የማያልቅ እውቀት አለ። ከአንድ የህክምና ዶክተር በተሻለ የባህል መድሃኒተኞች ስለ በሽታ እና መድሃኒት የተሻለ እውቀት አላቸው፣ ከታሪክ ባለሙያዎች ባልተናነሰ መልኩ ሽማግሌዎት የማያልቅ ታሪክ ያውቃሉ፣ ከግብርና ባለሙያ በተሻለ አርሶ አደሮች ስለ ምርት እና አፈር ምንነት ያውቃሉ። ልየነቱ ቀለም የማወቅ እና ያለማወቅ ጉዳይ ካልሆነ በቀር።

አብዲሳ አጋ

እጅ እና እግሬን የፊጥኝ አስረው ከፎቅ ላይ ወረወሩኝ። በታዕምር ተረፍኩ። ፓሊስ ጣቢያ ወሰዱኝ። ውሃ በላየ ላይ እያፈሰሱ እስኪበቃቸው ደበደቡኝ። ውሃውን በላየ ላይ ለቀውት ሲፈስብኝ አደረ።በዚያ ላይ መሬቱ ሲቢንቶ ነበር። ጠዋት ሲመጡ "ይሄ ጥቁር አልሞተም" ብለው በመስኮት አይተውኝ ይሄዳሉ። የህዝቡ መገደል የአላግባብ ደም መፍሰስ ያሳዘነኛል። ይቆጨኛል። ከአዲስ አበባ ሞቃዲሾ፤ ከሞቃዲሾ ጣልያን ናፓሊ በመርከብ ነው የሄድንው። ናፓሊ ውስጥ አኛ የሚባል እስር ቤት ገባን። ተለይቶ የተዘጋጀ ቦታ ነው። እዚያ ሆነን የእንግሊዝ መንግስት ወረቀት ይበትን ነበር። የእነ ሃይለስላሴን፣ሩዝቬልት፣ናፓሊን እና የመሳሰሉትን መሪዎች ስም የያዘ ነው። ይህንን ወረቀት ይዟል ተብየ ሰደበደብ መሞቴ ካልቀረ ብየ ወታደሩን መልሼ መታሁት። ይሄ ነው ከፍተኛ ድብደባ የዳረገኝ።
ስር ቤት እያለሁ ለማምለጥ ከፍተኛ ጉጉት ነበረኝ። ጁሌት የሚባል ዩግዝላቪያዊ ጓደኛየም ይህንን ያስብ ኖሯል። 3ኛ ፎቅ ላይ ነበር የታሰርኩት። አንድ ቀን አቅሮፕላን መጥቶ ሲደበድብ አጋጣሚውን አግኝተን በመብራቱ ታግዘን ከ3ኛ ፎቅ ብርድ ልብስ ቀድጄ በእሱ ወርጄ ከጄሌት ጋር አመለጥን። ወደ ሳንቢችኖ ተራራ ለመድረስ ስንጓዝ አደርን። በማግስቱ ደረስን። በኋላ እንግሊዛዊው አዛዥ ሜጄር ፋይልን
"እዚያ ብዙ ኢትዮጵያኖች እና ዩጎዝላቪያን እስረኞች አሉ እነሱን ማስፈታት እንፈልጋለን። እነሱን እናስለቅቅና መሳሪያም እንዝረፍ " ብለን መሳሪያ እንዲሰጠን ጠየቅን።
" ይሄ ይፈፀማል ብየ አለምንም ግን ውሰዱ" ተብለን ተፈቀደልን። እዚያ ከነበሩት ኢትዮጵያዊያን እንግሊዛዊያን እና ዩጎዝላቪያን ውስጥ 30ዎቹ ወደ እስር ቤት ሰበራው ለመሄድ ተስማሙ። እጃችን ላይ የነበረው መሳሪያ 1ሳንጃ፣ አንድ አልቤን ክላሽ፣አንድ የእጅ ቦንብ እና 2ክላሽ ነው። እስር ቤቱ 75ኬ.ሜ አካባቢ ይርቃል። እስር ቤቱ ለመድረስ ትንሽ ሲቀረን እና ትሬያ የምትባል ከተማ ስንደርስ ስልክ እና መብራት እንዲቆረጥ አደረግን። እስር ቤቱ ደረስን። እኔ እና ዱገላስ በደረታችን ተስበን ወደ ዘቡ ስንጠጋ ዘቡ በቁሙ እንቅልፍ ይዞት አየን። ዱገላስ በተክለ ሰውነት ገዘፍ ስለሚል አንገቱን ሲይዝልኝ እኔ ጠመንጃውን እና እግሩን ይዤ ወደ ጉድጓድ ውስጥ ወስደን ገደልንው። ዱገላስ የዘቡን ልብስ ለብሶ እንዲቆም አደረግን። ሌላ ዘብ ደግሞ ለቅያሬ መጣ። ያንንም ዘብ ገላገልንው። ሌላኛውን ዘብ ያዝንና መሳሪያችንን ወደ 3 ከፍ አደረግንው። ዘብ ቤት ሄደን የሁሉንም መሳሪያ ወሰድን። አንደኛውን ዘብ "የወህኒ ቤቱ ሃላፊ ወዳለበት ቦታ ውሰድን" አልንው። አማራጭ ስላልነበረው ወሰደን። ማርሻል ሎጄስቴሬኢያሪኮ ይባላል።
"ማርሻል" ብሎ ተጣራ።
"አቤት" አለው
"ከታች ብዙ ድምፅ ይሰማኛል ምንድነው?" አለው
"መብራትም ጠፍቷል ምን ይሆን" ብሎ ተነሳ። ብቅ ሲል በመትረየስ መታሁና ጣልኩት። ሚስቱ እና ልጆቹ መንጫጫት ሲጀምሩ እነሱንም ጭረስናቸው። እስረኞቹን በሙሉ አስፈታናቸው። ምግብ፣ ልብስ እና በርካታ መሳሪያዎችን ዘረፍን እና መሄድ የፈለጉትን እስረኞች ይዘን ወደ ቦታችን ተመለስን።
.....አንድ ቀን የጀርመን ናዚ ወታደሮች በአውሮፕላን እኛ ከሰፈርንበት ቪያኖራ ቦታ አረፉ። ቦታውን ለመሰለል ኖራል የመጡት። አንዱን ያዝንው እና ሁሉቱን አውሮችላናቸውን አስነስተው አመለጡን። የተያዘውን ሰው ምርመራ አደረግንበት።ዮጎዝላቪያዊው ሜጀር ጁሌት ጀርመንኛ ጥሩ አድርገጎ ይናገር ስለነበር የመጡበትን ምክንያት ጠየቀ።
"እዚህ ቦታ አርበኞች ስላሉ እነሱ ያሉበትን ቦታ አይተን በሌላ ግዜ በእግረኛና በአውሮፕላን ለመደብደብ ነው ብሎ" ይመልሳል። "ይሄ ፍርድ ያስፈልገዋልና ፍርድ መሰጠት አለበት" ብለን ወሰንን። እንግሊዛዊው ሜጀር ፋይል እንዲደበደብ አዘዙ። የምትፈልገውን ተናገር ሲባል
"አንደኛ በሌላ ሰው እጅ እንዳልደበደብ በኢትዮጵያዊው አንቶኒ(አብዲሳ) እጅ መሞት እፈልጋለሁ።ሁለተኛ መሳሪያየን ለእሱ መታሰቢያ ስጡልኝ" ብሎ ተነገረ። ከዚያ ደግሞ "አንድ ቃል ልናገር ብሎ መንግስቴ ለዘላለም ይኑርልኝ" ብየ ልናገር ብሎ ተፈቀደለት።
..... ድል አድርገን ሮም ስንገባ 400 ወታደሮች ሁሉም የውጭ ሃገር ዜጎች ናቸው የእንግሊዝን ባንዲራ በቀኝ ክንዳቸው የኢትዮጵያን ባንዲራ በግራ ክንዳቸው ላይ እንዲያስሩ አደረኩ። እኔ የምፈልገው የኢትዮጵያ ቀለም እዚያ መገኘቱን ነበር።
..... እዚያ በእኔ ስም ሽፍቶች ሃገሬውን ይዘረፉ ነበር። ተከታትየ በህይወታቸው ቀጣኋቸው።
...... እዚያ ሆኜ እናቴም አባቴም ወንድሞቼም አይደሉም የሚናፍቁኝ። ሃገሬ ብቻ ነበረ የሚናፍቀኝ። ሃገሬ ነው
አብዲሳ አጋ ከኢትዮጵያ ራዲዩ ጋር ካደረጉት ቃለመጠይቅ የተወሰደ
"አንሶላ የተጋፈፍኳቸውን ሴቶች ቁጥር አላስታውስም። ቆንጆ ከሆነች እንድታመልጠኝ አልፈልግም። ሁሉም ቆንጆ ሴቶች ሚስቶቼ ቢሆኑ እመኛለሁ። በተለይ ይሄ የሹፍርና ስራየ ቀላል አልተመቸኝም። ማርሽ አስገብቼ እጄን ጋቢና ካስቀመጥኳት ልጅ ጭን ላይ ጣል አደርገዋለሁ። ዝም ካለች ጨዋታው ይቀጥላል። ካላለች ሌሎች ስልቶች ይከተላሉ።" አለኝ በታሪፍ ተጣልተን በኋላ ምርጥ ጓደኛሞች የሆንን አንድ ሹፌር። ጋቢና ሰው አለ ሲል ቆይቶ ሊሞላ አንድ ሰው ሲቀር ደርሼ ነው ያስገባኝ። "ምን እንደሚያስጠልኝ ታውቃለህ?" አለኝ።
"አላውቅም" አልኩት።
"ሌዘር የሚለብስና ሳምሶናይት ቦርሳ የሚይዝ ሰው" አለኝ። ፈገግ አልኩለት እና
"ለምን"አልኩት።
"በቃ አጉል መብቴ ይከበር ባይ ናቸው። የእኛ ስራ ውጣ ውረዱ አይታያቸውም። በጣም ስለሚያበሳጩኝ እንደዚያ ያሉ ሰዎችን አልጭንም" አለኝ።
"ስራችሁማ ምን ውጣ ውረድ አለው። የፈለካትን ሴት እያሳደድክበት.." አልኩትና ሳልጨርስ አቋረጠኝ
"እሱስ ልክ ነሽ አባየ! ስንቱን በላንበት መሰለሽ። ጥቅሙ ይሄ ብቻ ነው። እንጂማ ትራፊክ በያዘህ ቁጥር የቀን አበልህን ለመንግስት እየገበርክ እንዴት ትችለዋለህ?" አለኝ።
"ዛሬ ግን ጋቢና ቆንጆ ሴት ባለመጫንህ ቅር አላለህም?" አልኩት።
"ቀላል ብሎኛል! ሴቶች በጣም ነው ደስ የሚሉኝ። ደግሞ መሪ የያዘ ወንድ በጣም ይወዳሉ። እኔማ ጋቢና ሴት ካስቀመጥኩ ችግር አለብኝ። ለምን ትልቅ ሰው አትሆን መነካካቴን አልተውም። አንድ ግዜ ወደ ደሴ ስንሄድ መሽቶ ሁሉም ተሳፋሪዎች እንቅልፍ ያዛቸው። ጋቢና የተቀመጠችውን ሴት ነካክቻታለሁ። እጄን ማርሽ እየቀየርኩበት አስመስየ ጡቶቿን ሳይቀር አሸሁላት። እሷም የምትሆነውን አሳጣት። ቀስ ብየ መኪናውን ዳር አስይዤ አቆምኩትና ለሽንት እንደሚወርድ ሰው ወረድኩ። እሷም ገብቷታል ወረደች። በጀርባ በኩል ስዞር ሰዎቹ ከእንቅልፋቸው እየነቁ የመኪናው መቆም ግራ ገብቷቸው መጋረጃውን ገለጥ ገለጥ ማድረግ ጀመሩ። በብስጭት ገብቼ መኪናየን መንዳት ጀመርኩ" ብሎ መሪውን በመዳፉ መታ አደረገው። ሲያወራ እያዝናናኝ መጣ። ስሜቱን በጭራሽ መደበቅ አይችልም። ሲበዛ ግልፅ ነው። ወሬው ደግሞ ከሴትና ወንድ ወሬ እንዲወጣበት አይፈልግም።
"አንድ ግዜ ደግሞ ባልና ሚስቶች ኮንትራት አድርሰኝ ብለውኝ ጉዞ ጀመርን። ጋቢና መጥተው ሁለቱም ተቀመጡ። ልጅቷ እንዴታባቷ እንደምታምር አትጠይቀኝ። ረዳቴ ከኋላ ወንበር ሄዶ ተኝቷል። ቀኑ እየመሸ ሲሄድ ባልዮው እንቅልፍ አዳፋውና ከኋላ ልተኛ ብሎ ሄደ። ረዳቱ ቦታ ለቀቀለትና አስተካክሎ አስተኛው። ረዳቴ ጋቢና መጥቶ ልጅቷን መሃል አስቀምጥናት። አባየ.. ጨዋታው ተጀመረ። ልጅቷን ከጭኖቿ ጀምሬ ስደባብሳት ፈፅሞ ልትከለክለኝ አልዳዳታም። ረዳቴም ይነካካ ኖሮ ዝልፍልፍ ማለት ጀመረች። ቆይቼ ረዳቱን አስትቼ ነገሩን ጋብ አደረግንው። አንዲት ከተማ ደረስን። መኪናውን ጥግ አስይዘን እራት እንደሚበላ ሰው ሆቴል ገባን።.."
ወሬውን እንደቀጠለ ስልኬ ድንገት ጠራ። ይህንን እያወራኝ ስልክ አንስቶ ነገር ማቆርፈድ መስሎ ቢታየኝም የስራ ስልክ ስለሆነ ማንሳት ግዴታ ሆነብኝ።
"ሄሎ"
"ደህና ዋልክ አዲስ ማታ ስራ መግባት አለብህ" ተባልኩ። መመለስ አለብኝ ማለት ነው።
"ሹፌር ስራ ገጠመኝ ወደ አዲስ አበባ ልመለስ ነው። መኪና አስቁምልኝ" አልኩት። መኪና አስቁሞልኝ ወደ አዲስ አበባ ጉዞየን ጀመርኩ። የልጁ ድርጊት ግን ከአዕምሮየ ሊወጣ አልቻለም።...

"አርሶ መራብና ተኩሶ መሳት እያድር ይፋጃል እንደ እግር እሳት"

"አባቴ ሰይጣንን የሚያመልክበት ጎጆ ቤት ነበረው። የሆነ ወቅት ላይ ቤቷ ፈረሰች። ሰይጣንም አባቴን ቤቴን ካልሰራህልኝ ደመራን አላሳልፍህም እግድልሃለሁ አለው። አባቴ ነገሬ ሳይለው ተወው። እንደተባለው አባቴ ሆዴን ወጋኝ ብሎ ከዚህ ዓለም ተለየን። በዚያው ሳምንት እናቴም ሆዴን አመመኝ ብላ ለሞት በቃች። እኔ፣እህቴ እና ወንድሜም የትም ተበተንን። የምንበላው እና የምንለብሰውን ሰዎች እየመፀወቱን በነፍስ ለመቆየት ያክል እንኖራለን" አለች እና እንባዋ ዝርግፍ ብሎ ወረደ። ያሳዝናሉ። ኑሯቸው ከመቃብር በታች የሆነ ያክል ነው። እነዚህ ልጆች የሚኖሩት ከደብረ በረሃን በግምት 25ኪ.ሜ ከምትርቅ ቀይት ከምትባል ከተማ ውስጥ ነው። ምግባቸውን መምህራን በየተራ እያመጡ ይሰጧቸዋል። ለዚያውም ካልሰለቹ!! ከደሞዛችን ያዋጣናትን እና Hirut Negesue ሂሩት ነገሰ ሰብስባ የላከችልንን ገንዘብ ከፋፍለን የ2ወር ቀለብ እንዲገዛላቸው አደረግን። ሆድ እየጮኽ ትምህርት እና ለውጥ እንዴት ሊታሰብ ይችላል? ልጆቹ ይቺ ተደረገችልን ብለው ፈጣሪ ከሰማይ የወረደላቸው ያክል ተደሰቱ። አንጀት ይበላሉ።
ጓደኞቻችን Misahun Negash እና ይርጉ ኃይለማሪያም የመለመሏቸው ሌሎች ችግረኞች ቤት ሄድን። ከዚችው ከተማ * ኪ.ሜ አካባቢ ወደሚርቅ እና አዲስጌ ወደሚባል ቀበሌ። እዚህም ሌላ ችግር በሰዎች ላይ አፉን ከፍቶባቸዋል። እዚህ ቤት አንድ ልጃቸው ችግር አስመርሯት ወልዳ አራስ ልጇን ትታ በገመድ ታንቃ ሞተች። እናት ከሃዘን እና ከችግር ጋር የልጅ ልጇን ማሳደግ ተፈረደባት። የወላድ አንጀት ይሄን እንዴት ይቻል?
"አርሶ መራብና ተኩሶ መሳት
እያድር ይፋጃል እንደ እግር እሳት" የሚለውን ግጥም አስታወስኩትና አጥንቴን ሰርስሮት ገባ። ችግር እና መጎሳቆል ሰው ፊት ላይ ሲነበብ ማየት ህመሙ ከተቸገሩት ሰዎች የሚተናነስ አይመስለኝም። ቤት መኪና ምናምን መመኘቴን እርግፍፍ አድርጌ ተውኩት። የችግራቸውን ሁኔታ አንድ በአንድ ነግሬ ሌላ ሃዘን እንድጨምርባችሁ ስለማልፈልግ ልዝለለው። ብቻ እዚህ ቤትም ትንሽ ነገር ተደረገችልን ብለው እንባ ተናነቃቸው። ገንዘቡን ለመስጠት ስንሄድ የቀበሌውን አስተዳዳሪ እንዲገኝ አድርገን ስለነበር ነፃ የህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ የድጋፍ ፍቃድ እንዲሚሰጧቸው እና የገንዘብ ድጋፍ ሊያደርጉላቸው እንደሚችሉም ቃል ገቡልን። እኛ በሰበሰብናት ሚጥጥየ ገንዘብ ሰዎችን ማነሳሳት መቻላችን ትልቁ ግብ አደረገን ወሰድንው። እዚያው ወረዳ ላይ ሙሽ የሚባል ቀበሌ ላይም ሌላ ችግር ያነወዘው ቤተሰብም ጎበኘን። የሚያሳዝነው ሁሉም ቤት ልጆቹ ሲመረጡ የአካል ጉዳት እና ሌሎች ተያያዥ የጤና ችግሮች ያለባቸው ልጆች ነበሩ። የሆነው ሆኖ ባይጠቅምም ወገን አለን ብለው እንዲያስቡ ያደረግናቸው ይመስለኛል። እኛ ገንዘብ ኖሮን አይደለም ይህንን ያደረግንው። ብዙዎቻችን ከቤት ኪራይ የሚያልፍ ደሞዝ የለንም። ስንሰባሰብም ከደሞዛችን በወር 1መቶ ብር ብንለግሳቸው ብለን ነው። ይበዛብናል ሳንልስ እንቀራለን!? ከሁሉ ነገር የሚበልጥ ሰውን የመርዳት ወኔ ግን ነበረን። እነዚህ ልጆች ትንሽየ ከተማ ውስጥ ለቤት ኪራይ በወር 30 ብር የሚሰጣቸው ሰው ከምንም በላያቸው ነው። ከተማ ውስጥ ጎዳና የወጡ ሰዎች እኮ በቀን እጁን የሚዘረጋላቸው ሰው አያጡም። ገጠር ውስጥ ያሉት ግን ስለመኖራቸውም አይታወቁም። ተራፊ የሚሰጣቸው አይኖርም። የአብዛኛው ህዝብ አኗኗር ከዚህ ጋር የሚቀራረብ ቢሆንም እጅግ የባሱትን ማየት ሁሉ ነገር ውሸት መሆኑን ማንም ሰው ይረዳል። በቃ አሁንም ድሃ ነን። እልም ያልን ድሃዎች። የሆነው ሆኖ ቀጣይ ፕሮግራም ይኖረናል። ባናግዛችሁ እንኳ የልጆቹን አኗኗር አይተን በሃሳብም ቢሆን እንረዳዳለን የምትሉ ካላችሁ ቀጣይ ላይ አብረን ተጉዘን ኑሯቸውን አይተን መመለስ እንችላለን። ከአዲስ አበባ ደርሶ መልስ 120 ብር ቢፈጅ ነው። ሰዎች ያድርጉ ከማለት እኛም ትንሽየ ነገር ብናደርግ የአዕምሮ እርካታ ነው፤የማህበረሰብ ድጋፍ ነው፣የዜግነት ግዴታችንን መወጣት ነው፤ህዝብ መውደድ ነው፤ህዝብን መውደድ ደግሞ ሃገርን መውደድ ነው። ህዝባችንን ሳንወድ እና ማገዝ እየቻልን ባናግዛቸው ሃገሬን እወዳለሁ ብንል ትርጉሙስ ምንድነው? አድራሻችሁን ብታስቀምጡልን አንድ ቀን በሚኖረን የደርሶ መልስ ጉዞ አብረን መጓዝ እንችላለን!!
#ሼር ብታደርጉና ለወዳጆቻችሁ ብታደርሱልን ደጋግ ሰዎችን እንድናገኝ ያግዘናል። እናንተም ይህንን ስታደርጉ ሰዎቹን እንደረዳችኋቸው ቁጠሩት።
መልካም ግዜ
8የደብረ ብረሀን ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች አባይ ባንኮችን ይሄዱና የደንበኞቻችሁን ገንዘብ የምታንቀሳቅሱበት ሲስተም ለዝርፊያ በቀላሉ ይጋለጣልና እኛ ደህንነቱን የሚያስጠብቅላችሁ ሲስተም እንዘርጋላችሁ ይሏቸዋል። "አሁን እናንተ.." በሚል አንፈልግም ይሏቸዋል። ልጆቹ "ለምን አናሳያችሁም" ብለው ሲስተሙን ሰብረው 80ሺ ብር አውጥተው ይጠቀሙበታል(ተመቹኝ)። በዚህ ምክንያት ልጆቹ በቁጥጥር ስር ዋሉ። እኔ ግን እነዚህን ልጆች ከማሰር እውቀታቸውን መጠቀም የሚሻል ይመስለኛል። በነገራችን ላይ ዩኒቨርሲቲው ውስጥ እሳት የላሱ ልጆች ሞልተዋል። አንደኛው ልጅ የግዕዝ አማርኛ መተርጎሚያ ሶፍትዌር አዳብሯል። ቀጣይ አመት ወደ ስራ ሊያስገባው እየሰራ ነው። ሌላው ደግሞ ከአፈር ኤሌክትሪክ ማመንጨት የሚያስችል ስራ ሰርቷን። አንዱ የፊዚክስ መምህር ደግሞ ሊባረሩ ጫፍ የደረሱ ተማሪዎችን ተቀብሎ በማስጠናት ለውጤት አብቅቶ ከልጆቹ ጋር በመሆን ከቆሻሻ ከሰል እያመረተ ነው።
ሌላ ደግሞ እዚያው ደብረ ብረሃን የሆነውን ልንገራችሁማ.....
ልጁ ሹፌር ነው። ማንም የሚቀጥረው ሰው ያጣል። በመሃል አባቱ በጠና ይታመማሉ። ስለዚህ ያለኝ አማራጭ ብር መስረቅ ነው ብሎ ወደ አካሉ ሆቴል ያመራል። ይገባና 11ሺ 300 ብር ይዘርፍና ሊያመልጥ ሲል ፓሊሶች ይከቡታል። ጥበቡን ተጠቅሞ ተሰወረባቸው። ፓሊሶቹ ሆቴል ገብተው ፍለጋውን አጧጧፉት። ልጁ የለም። ከደቂቃዎች ፍለጋ በኋላ አንደኛው ግድግዳው ጥግ ያለውን ነጭ ነገር ከፈተው። አጅሬ 11ሺ 300 ብሩን እና ቢራ ታቅፎ ከተጋደመው ፍሪጅ ውስጥ ጥቅልል ብሎ ተኝቶ ኖሯል። አስቡት በደብረ ብረሃን ብርድ ፍሪጅ ውስጥ ገብቶ በረዶ ሸፍኖት አለመጥፋቱ!? ልጁን ወዳጄ alayu geremew አግኝቶ ሲያናግረው "አባቴን ለማዳን ስል ስርቆት ውስጥ በመግባቴ እና ስሰርቅ በመያዜ አልፀፀትም" ብሎታል።

ከቴም እቴ

ከስራ ስወጣ ወደ ቤት የሚሸኘኝ ሹፌር ካለወትሮው ሌላ መንገድ መርጦ ውስብስብ ያለ ሰፈር ውስጥ ይዞኝ ገባ። ለምን እንደሆነ ስጠይቀው "እቃ ተቀብለን ወደ ቤት ላደርስህ ነው" አለኝ። ተስማማን። ወደ ሰፈር ልንደርስ ስንል ቁልቁለት ነገር ኑሮት እንደገና ዳገት ያለው ቦታ ገጠመን። ይቺን ለመውጣት ከታች መንደርደር ያስፍፈልጋል። ቁልቁለቷን ጨርሰን ዳገቷን ስንጀምር የመኪናው ሞተር ድርግም ብሎ ጠፋ እና ሚኪናው ወደ ኋላ ተመለሰ። ሞተር አስነስቶ አሁንም ሊንደረደር ሲል ሞተር ይጠፋበት ጀመር። በ3ኛው ሲወጣ የሼፌሩን እግር ፔዳል አረጋገጥ ማየት ጀመርኩ። ዳገቱን ሲጀምር ፍሪሲዮን ሳይረግጥ ፍሬን ቶሎ ሲይዝ እና ሞተሩ ጠፍቶ መኪናው ወደ ኋላ ሲመለስ አየሁ። ይሄ ጠፍቶት ነው ብየ ባላስብም "ውረድ እና እኔ ላስጣልህ" አልኩት። አይሆንም ብሎ ድርቅ አለ። "
እንዲያውም አንተም ስለደረስክ በእግርህ ወደቤት ሂድና ምሳህን ብላ እኔም መኪናውን ወደ ኋላ ወስጄ ጥግ አስይዤ እቃየን ልቀበል" አለኝ። ነገሩ ሁላ ባያሳምነኝም ተስማማሁ። ዳገቷን ወጣ ብየ ወደ ቤት መግቢያየ እጥፍ ስል ከየት መጡ ሳልላቸው የሆኑ ሰዎች አፋፍሰው መኪና ውስጥ አስገቡኝ። መጀመሪያ በጃኬታቸው አይኔን ሸፍነውኝ ነበር። መኪና ውስጥ በሆነ ጨርቅ ነገር አይኔን ብቻ አስሩና እጄን ወደ ኋላ በካቴና ነገር አሰሩኝ።አንዳቸውንም ማየት አልቻልኩም።
"ስንነግርህ አልሰማ አልክ አይደል?" አለኝ አንደኛው። መኪናው እየሄደ ነው። ወዴት አቅጣጫ እንደሚሄድ መለየት አልቻልኩም።
"እንዴየ ምን አደረኩ ቆይ? ምን ነግራችሁኛል? ልትዘርፉኝ ከሆነ ያው ያለውን ውሰዱና እኔን ልቀቁኝ" አልኩ ልቤ እየመታ።
"ሂድ!! የማትረባ። አንተ አሁን ምን ኖሮህ ነው የምንሰርቅህ?" አለኝ።
"ከአንዴም ሁለት ግዜ ሰው ላክንብህ። አንተ ግን አሻፈረኝ አልክ" አለችኝ አንዷ ሴት።
"ስለምንድነው የምታወሩት"ብየ ተበሳጨሁ።
"እሱን ስትገረፍ ታውቀዋለህ" አለኝ ከጋቢና በኩል የተቀመጠ ሰው፡ ሹፌሩ ይሁን አይሁን ግን መለየት አልቻልኩም። ወዴት እየወሰዱኝ እንደሆን ለመለየት ጥረት ባደርግም አልተሳካልኝም።
"አራት ኪሎ፤ አራት ኪሎ፤ ቦሌ፤ ቦሌ የሚል የወያላ ድምፅ ሰማሁ። ወዲያው መስኮቶቹን ሲዘጉብኝ ድምፅ መስማት ሳልችል ቀረሁ።
"እናታችሁን ልቀቁኝ" ብየ እሪታየን ሳቀልጠው አንዱ
"ዝም በል ክፍት አፍ" ብሎ ጨርቅ አምጥቶ አፌ ላይ ወተፈብኝ። እግራቸው ማስቀመጫ ጋር አስተኙኝና እግራቸውን አስቀምጡብኝ። የአንደኛው ሰው እግር ሸተተኝ። ወደ ላይ ልበልህ አለኝ። አፌ ታፍኖላልና በደንብ በማይሰማ ድምፅ
"እናትህንና ጫማህ ይሸታል" አልኩት ለመገላበጥ እየሞከርኩ። እንደመሳቅ አሉና
"ገና የሽንት ቤት ቀዳዳ ውስጥ አንገትክን አስገብቼ እረግጥሃለሁ" አለኝ። በጫማው ቆሻሻ ረግጦ ኖሮ
"ወርደህ ጥርገህ ና" ምናምን አሉት።
"ስንደርስ በዚህ በማይረባ ሰው ጃኬት እጠርገዋለሁ" አለ። መናገር አልቻልኩም። ምን እየተሰራ እንደሆነ ማወቅ አልቻልኩም። እንኳን ለማምለጥ ለመጮህ እንኳ እንዳልችል አድርገውኛል። ሹፌራችን እጁ እንዳለበት ጠረጠርኩ። ከቢሮ ስንወጣ ሌሎች ሰራተኞችን እግረ መንገዱን ይዞ ይወጣ የነበረ መኪና ማንንም መጫን ሳይፈልግ እኔን ብቻ ይዞኝ እንዴት ሊወጣ እንደቻለ ግራ ገባኝ። መንገዳችን ላይ ይወርድ የነበረ ሰውም "ይዘህኝ ሂድ" ብሎት "ወደ ሌላ ቦታ ነው የምንሄደው" ብሎ እምብይ ብሏል። የተቀነባበረ ነገር እንዳለ ገባኝ። እንዴት እንዲህ አሳልፎ ይሰጠኛል? ዝም ብየ ማሰላሰል ጀመርኩ። አወጣለሁ አወርዳለሁ፥ ምንም ጠብ የሚል ሃሳብ ጠፋ። ይልቁንም ቀኑ የተወለድኩበት ቀን መሆኑ የባሰ አባሳጨኝ። መኪናው የሚያንገራግጭ መንገድ ውስጥ ገብቶ 5 ደቂቃ ያክል ከተጓዘ በኋላ አንድ ግቢ ውስጥ ገባ።
"አውርዱት" አለ መኪና ውስጥ ያልነበረ ሰው ይመስለኛል። አውረደውኝ ግራና ቀኝ ይዘው ፀጥ ወዳለ ቤት ውስጥ ይዘውኝ ገቡ።
"መጀመሪያ ይገረፍ ወይስ ቃሉን ይስጥ?" አለ አንደኛው።
"ሱሪውን አውልቀን እንግረፈው" አለች አንዲት ሴት። 'ድሮም ሴት አይሆነኝ ወይኔ ጉዴ አለቀልኝ በቃ' አልኩ በውስጤ። አፌ ውስጥ ጨርቅ ተወትፎ "ምን አድርጌ ነው ማለት እንኳ አልቻልኩም።
"ከአፉ ላይ የወተፋችሁትን ጨርቅ አውጡለት" አለ። የአብዛኞቹ ተናጋሪዎች ድምፃቸው ጎርነን ያለ ነው። ሆን ተብሎ የተደረገ እስኪመስል።
"የህዳሴው ግድብ ከዳር እንዳይደርስ ከግብፅ ጋር አሲረሃል" አለቸኝ ያቺ ቅልብልብ። ልክ ቲያትር እንደሚሰራ ድምፁዋን የሆነን ሰው ለማስመሰል የሞከረች ትመስላለች። ከት ብየ መሳቅ ስጀምር በጥፊ አጋየችኝ።
"እናትሽ ት..." ብየ ጮኩባት። በውስጤ 'ይሄ አጉል ልማድ' ብየ በስድቤ ተፀፀትኩ። 'በቅሎ ማስሪያዋን በጠሰች ቢሏት ወዲያው አሳጠረች' ብየም ተረትኩ።
"እግሩን ወደ ላይ አድርጋችሁ ስቀሉልኝ" አለ አንደኛው።
"ቆይ ቆይ መጀመሪያ የኢሜል እና የፌስ ቡክ አካውንቱን ከነፓስወርዱ ይስጠን" አለና ወረቀት ማገላበጥ ጀመረ።
"ኢሜልክን ተናገር" አለኝ።
" እናንተ ማን ናችሁና ነው የምነግራችሁ?"
"ሰውነትህ እንዲተለተል ከፈለክ አለመናገር መብትህ ነው" አለና አንባረቀ። ወዲያው
"አንተ ልብሱን አውልቅልኝ። አንቺ አልንጋውን አምጪ" ብሎ አዘዘ። ደንዝዣለሁ። አንደኛው መጥቶ ጃኬቴን እና ቲሼርቴን አወለቀ።
"እሺ እሺ ልስጣችሁ" ብየ ተስማማሁ።
"ኢሜልክን ተናገር አለኝ"
"addismekonen@yahoo.com" አልኩት።
"ፓስዎርድ" አለኝ። ሳልመልስ ዝም አልኩ
"ተናገር እንጂ" አለኝ።
"a..."
"እየጠበኩህ ነው" አለኝ
"m...."
"ቀጥል ቀጥል " አለኝ። ያቺ ቅልብልቅ መጣችና
"አለቃ ምርመራውን አቁሙት ተበሏል፦ከበላይ" አለች።
"ተባለ እንዴ? ምን ይቀልዳሉ ግን? በቃ ልብሱን አልብሱና ፍቱት" አላቸው። አቋቋሜን አስተካክለው ልብሴን አለበሱና የሱሪየን አቧራ አራገፉልኝ። እጄንም ፈቱልኝ። ኮሌታየን አስተካከሉልኝ። ፀጉሬንም አበስ አበስ አደረጉና አስተካክለው አይኔን የሸፈኑበትን ጨርቅ አነስተው
"Happy Birth Day to you" በለው ቀወጡት። እየተበሳጨሁ ኬክ ቆረስኩ። ወደ ሞት እየተጠጋን እንደሆነ ለሚነግረን እድሜ ሞት ሞት በሸተተ "ሰርፕራይዝ" ተቋጨ። በጥፊ የመታችኝን ማርታን በኬክ ጠፍጥፌ ጣልኳት። "ድንቄም ሰርፕራይዝ!"
ይቺ አስማት የሆነች ሃገር አንኳን ህዝቦቿ አፈሯም እንዲህ ይናፍቃል፡፡ ሃገርክን የካድህ ሁላ አንድ ቀን በናፍቆት አፈሯን ስመህ ሳይሆን በፀፀት ይቀር በይኝ ብለህ እግሯ ስር ትወድቃታለህ፡፡ ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር፡፡

ኢትዮጵያ እንደ ቻይና


የባህረ ሰላጤው ሃገራት ኳታርን አየር ላይ ሲያንሳፍፏት፥ ኳታር ግራ ቀኙን ስታይ በዚያ ሳውዲ፣ በዚህ ግብፅ ፤ እና ደግሞ ዩናይትድ አረብ ኢሚሬቶች እና ባህሬን ሲያድሙባት አይኗን አሻግራ ጦቢያችን ላይ አሳረፈች። አሳርፋም አልቀረች የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሯን "እንደ አሞራ በርርህ ጦቢያ ደርሰህ ና" አለችው። ሰውየው አዲስ አበበ ከተፍ አሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማሪያምን "ሃይለየ የባህረ ሰላጤው ሃገራት አደሙብን። ጁቡቲ እንኳ ከአቅሟ ከአነ ሳውዲ ጋር ሄዳ ተለጠፈች። አገራችሁ ከጎኔ ትሰለፍ ዘንድ እባክዎ ቃልዎትን ይስጡኝ" ብለው ለመኑ። ጦቢያየ በሃይልሻ በኩል "እኔ ሁላችሁችም ወዳጆቼ ናችሁ። ስለዚህ ችግራችሁን በዲፕሎሞሲያዊ መንገድ እንዲፈታ የተቻለኝን አደርጋለሁ" አለች። እደጊልኝ ጦቢያየ!! በቻይና እቀና የነበረው ዓለም ላይ ችግር ሲፈጠር እና ኃያል ነኝ ባዩዋ አሜሪካ " ቻይንየ ከጎኔ ተሰለፊ" ስትላት "ጉዳዩ በሰለም እንዲፈታ የበኩሌን አደርጋለሁ" በማለት የምትመልሰው ነገሯ ነበር። ባለፈው እንኳ ያ ትራምፕ የሚሉት ሰውየ በሰሜን ኮሪያ ላይ ደነፋ ደነፋ እና ምንም ማደርግ ሲያቅተው "ቻይና ምነው ዝም አልሽ?" ሲላት ቻይንየ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሯ በኩል "የሰሜን ኮሪያ የኒውክለር ጉዳይ አሳስቦኛል። በጠረጴዛ ዙሪያ እንዲፈታም የበኩሌን እወጣለሁ" አለች። ማን በሰው ጉዳይ ፈትፍቶ ቂም ይሸምታል? የሰሞኑ በኳታር የኢትዮጵያ አቋምም ልክ እንደ ቻይንየ ተመችቶኛል። "ጉዳዩ በሰላም እንዲፈታ ኢትዮጵያ የበኩሏን ትወጣለች።" አለቀ!!
እንዲየው ከጭቆና አትቁጠሩብኝ እንጂ እኔ ግን ስለ ኳታር ትንፍሽ ሳይል በሌሎች ሃገራት የውስጥ ጉዳይ ገብቶ እየፈተፈተ ያስቸገረው አልጄዚራ ላይ ሁሉም ሃገራት ተባብረው አፉን ቢያዝጉት እንዴት ደስ ባለኝ። BBC እኮ በውጭ ሃገራት ላይ እንደፈለገ ቢዘል እንግሊዝንም ሳይምር ነው።

ቆጣስር

(የእሷ ባል የልጇ አባት ጠፍቶ ይህንን እያሰቡ ቢሆንስ)

ከአቡሸያ ጋራ ትመጣለህ ብለን
ጋራ ሸንተረሩን ሳንታክት አማትረን
ቅጠል በረገፈ ኮሽ ባለ ቁጥር
በብርሃን ፍጥነት ዞረን ስናማትር
አንተ ግን የለህም ድምፅህ አይሰማም
በኮሽታ ውስጥም መልዕክት አይደርሰንም።
እኔ ምን አውቃለሁ ልቤ እንዲህ ይለኛል
እንዳልተነካ ሰው ገላጋይ ይሆናል
በየተራራው ጥግ አስቤዛ ፍለጋ
ማጀቱን ለመሙላት ቀን ከሌት ስ'ተጋ (ስትተጋ)
ቀኝ አልቀና ብሎህ
ምን ይዤ ልመልስ ብለህስ እንደሆን?
እኔ ምን አውቃለሁ
ልጄም እንደ'ኔው ነው
በነጋ በጠባ ደጁን ያማትራል
እጆቹን አጣምሮ ሁሌም ይቆዝማል
የልጅነት ሆዱ ባብቶበት ይሆናል
አንዱ ልቤ ደግሞ
ከፋት ተሽከሞ
እንዲህ ይነግረኛል
የዚያ ሰፈር ሰዎች
የሆኑ ገብጋቦች
ሰብል ነክቶባቸው
ወጥመዱን ዘርግተው
ግድለውትስ ቢሆን?
አበስኩ ገበርኩ ሰይጣን አይስማብን
ጆሮውም ይደፈን
ና አማትብ አቡሽየ እንዳይሰማ ሰይጣን
ያደርገው ፈጣሪ ከእሱ በፊት ሞቴን
......
ሰይጣን የገባበት ግራ ጎኔ ደግሞ እንደዚህ ይለኛል
በወረደው ፀጉሩ በተንዘናፈለው
በሳንቃው ደረቱ እቀፉኝ በሚለው
ጎምለል ጎምለል ሲል ገብቶ ከቆንጆ አይን
ከሞላው ማጀቷቆጣስር ለማደር ገብቶላት እንዳይሆን?
(ለአዲስ አበቦዎች መፍቻ ቆጣ ስር= ወንድ በሴቷ ንብረት ለመተዳደር ቤቷ ሲገባ ቆጣ ስርነት ይባላል።)

ኮለኔሉ መረጃ ከሰጡን ያምታቱብን


ኮ/ል አስጨናቂ ገ/ፃድቅ "አጨራረሱ እንደ አጀማመሩ ድንገተኛና ያልተጠበቀ የሆነዉና ለመወሳት ያልታደለዉ የኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት" በሚል ሆርን አፍየርስ ላይ የፃፉትን ተከታታይ ፅሁፍ ከእልህ አስጨራሽ ንበት በኋላ ጨረስኩት። የፅሁፉ አጠቃላይ ጭብጥ ጦርነቱ በእኛ ድል አድራጊነት እንደተጠናቀቀ እና አሰብ የኢትዮጵያ ህጋዊ ይዞታ እንደሆነና መመለስ አለበት የሚል ነው። ፅሁፉን ሚዛናዊ ሆነው አንዳንዴም ወገን እያደረጉም ቢሆን የፃፉት እሳቸውም እንዳሉት የአሰብ ጉዳይ መነሳት መንግስትን ያበሳጫል እያሉ ደፈረው መፃፋቸው ለእኔ ተመችቶኛል። አንዳንድ እንደ ህዝብ በጅምላ በእውነትነት የፈረጅናቸውን እውነት "እውነት አልነበረም" ብለው ለማሳመን የሄዱበት መንገድ ግን ለአንባቢ በጣም አታካች ሆኖ አግኝቼዋለሁ። በዚያ ላይ ፅሁፉ ውስጥ ሙሉ አንቀፅ እየተደጋገመ መገኘቱ ደግሞ በአንዳንድ ጉዳዮች የደከመውን አንባቢ የበለጠ ያበሳጫሉ። እስኪ ያምታቱብንን ነገሮች አለፍ አለፍ ብለን እንጥቀስ፦ ምናልባት ተጨማሪ መረጃ ሌላ ግዜ ሊጨምሩልን ይችላሉ ብለን ተስፋ በማድረግ።
#የጦርነቱ አሸናፊ፦ ሊደል ሃርት (Liddell Hart) “ድል የአሸናፊዉን ኢኮኖሚ ፣ወታደራዊ አቅምና ህብረተሰቡን የሚያደቅ ከሆነ ረብ የለሽ ነዉ” ይላል፡ ብለው በጠቀሱት ፅሁፋቸው ውስጥ አንባቢ የጦርነቱ አሸናፊ እኛ ነን ብሎ እንዲያምን ሲያስገድዱት ይታያሉ። በዚህ ብያኔ መሰረት አንባቢ እንዴት የጦርነቱ አሸናፊ ነን ብሎ ሊያምን ይችላል? ወይ ኢሳያሳን ከስልጣን አላወረድን ወይ ባድመን ለእኛ አላስወሰንን ወይ አሰብን አልተረከብን.. በዚህ መሰረት ምንም ላላመጣልን ጦርነት ወንድሞቻችንን አጥተናል ብሎ ነው የሚያስበው አንባቢ። ኮለኔሉ ያስቀመጧቸው ማስረጃዎች እንዴት ሊገቡን ይችላሉ?
#የባድመ ጉዳይ፦ ባድመ ለእኛ ተወስኗል ተብሎ ህዝቡን አደባባይ አስወጥቶ በማስጨፈር የዓለም መሳለቂያ አድርገው ታሪክ ይቅር የማይለው ስህተት ተሰርቷል ይላሉ። ይህንን ያለው ደግሞ መለስ ሳይሆኑ ሌላ ሰው ነው ይሉናል። ፀሃፊው የኢትዮ ኤርትራ ጦርነት በታሪክ ትልቅ ቦታ ኖሮት ነገር ግን ያን ያክል አልተወሳም የሚል አቋም እስካላቸው ድረስ ባድመ ለእኛ ተወስኗል ያለውን ሰው በግልፅ ተናግረው ሰውየው መልስ ቢሰጥበት ታሪክ ነው እና ሁሉን እንደ ታሪክነቱ አንባቢው ተረድቶ ያልፈዋል። እውነቱም ለታሪክ ይቀመጣል። ያንን ግን በፅሁፋቸው አላስቀመጡትም።
=የአሰብ ጉዳይ፦ የፀሃፊው የአሁኑ አቋማቸው አሰብ የእኛ እንደሆነና መመለስ አለባት የሚል አቋም አላቸው። ለጉዳዩ ደግሞ አቶ መልስ ተጠያቂ ሊሆኑ አይችሉም። ይልቁንም በወቅቱ እሳቸዉ አሰብን በወታደራዊ ሃይል ለማስመለስ ሞክረን አልቻልንም ብለዉ ሲናገሩ አንድም ጀኔራል ወይም የጦር አዛዥ ወይም በዚያ ቦታ የነበሩ የፓርቲዉ ከፍተኛ አመራሮች መካከል አንዳቸዉም ለማስተባበል አለመሞከራቸዉ የመለስን አቋም ትክክለኛነት የሚያሳይ ነዉ፡ ብለው ፅፈዋል። ይህንን ማወቅ ከቻሉ በጦርነቱ ወቅት የእኛ ወታደሮች የጦር የበላይነት ተቀዳጅተው ኤርትራ ድምበር ገብተው ከፍተኛ የመደራደር አጋጣሚ ይዘው ጦርነቱን እንዲያቆሙ ያዘዘውን አካል ስለምን ለአንባቢ ነግረው ምላሽ እንዲያገኝ አላደረጉም?
በሌላ መልኩ
መለስ አሰብን ለማስመለስ በነበራቸዉ ፍላጎት መሰረት ለሰራዊቱ አዛዦች እንዲተገብሩት ትእዛዝ መስጠታቸዉንና ሰራዊቱ ግን ሞክሮ ለግዜዉ እንዳልተሳካለት በገለጹበት ወቅትም ይህንንም ያስተባበለ አንድም ጄኔራልና ኮሎኔል አልነበረም" ይሉናል። ይሄ ደግሞ የባሰ ግራ ያጋባል። በእልህ አስመራ ደረሰን የኢሳያስን ጆሮ ይዘን እንመጣለን ብሎ ግፋ በለው ሲል የነበረ የኢትዮጵያ ሰራዊት ተመለስ ተብሌ ወሽመጡ እንደተቆረጠ ነበር እስከ ዛሬ የተፃፉ መፀሃፎች የነገሩን። እና እንዴት ሆኖ ነው?
"መለስ ጄኔራሎቹን አማክረዉ ወደፊት ለመግፋት አንደማይችሉ መልስ ከሰጡዋቸዉ በኋላ ነዉ ዉሳኔዉን የወሰኑት፡፡(ጦርነቱ እንዲቆም) ብለውም ይነግሩናል።" ይሄ ሌላ ማጠናከሪያ ነው።
=የጦርነቱ ድንገተኛነት ፦ እዚህ ላይ አገም ጠቀም አይነት ትንታኔ ነው የሚሰጡት። አንደኛው ጦርነቱ ድንገት መጣብን ማለት ለማንኛውም ጦርነት ማለትም ጠላት አለ ተብሎ ነወይ የአንድ ሃገር ጦር ዝግጁ የሚሆነው ብለው ይወቅሱና እንደገና ኤርትራ ልትወረን የምትችልበት አንዳችም ምክንያት የለም ከሚል እሳቤ ነው ብለው ነገሩን ሊያመጣጥኑት ይሞክራሉ። በዚያውም "ኤርትራ ልትወረን ነው" ብሎ የተናገረን አንድ ሰው "ትምክህተኛ ነህ" ተብሎ ከስራ እንደተባረረ ነግረውን አንባቢውን ያምታቱል።
በሌላ በኩል
መከላከያ ሃይላችን የራሱ ዶክትሪን የሌለው ዘመናዊ መሳሪያ ያልታጠቀ እና ገና ራሱን እያደራጀ ባለበት ወቅት ነው ወረራ የተፈፀመብን ይሉና ዝቅ ብለው ደግሞ ኤርትራ ስለ እኛ የተሳሳተ ግምገማ በመያዟ ነው የተሸነፈችው ይላሉ። መከላከያችን ራሱን ገና እያደራጀ ከነበረ የኤርትራ ግምገማ ትክክል ነበር ማለት ነው። ለውጤቱ ምክንያቱ የራሳቸው ድክመት አልያም የኤትዮጵያውያን ጀግንነት ነው የሚል ድምዳሜ መሰጠት ነበር ባይ ነኝ። እዚህ ላይም አንባቢ ግራ ይገባዋል።
ሌሎች የሚያወዛግቡ ሃሳቦች
#እንኳን የኢትዮጵያ ህዝብ የኤርትራ ህዝብም ሳያስበው ነው ወደ ህዝበ ውሳኔ የገባው ይሉንና ቀጥለው ሻቢያ አስመራን ከተቆጣጠረ ከሁለት አመት መኋላ ሁለት ዓመታት ነጻነቱን ሳያዉጅ የቆየዉም የኢህአዴግን ፈቃድ ለማግኘት ብሎ ሳይሆን ለሪፍረንደሙ ቅድመ ዝግጅት ለማድረግ ግዜ ስላስፈለገዉ በራሱ ምክንያት ነዉ። የኤርትራ ህዝብም አበረው በዝግጅቱ ተካተው ነው የተፃፈው
#/ል ተወልደ ገ/ተንሳይ በፃፉት መፀሃፍ የጦርነቱን ድንገተኛነት የፃፉበትን መንገድ እንስተው የራሳቸውን አቋም አለመፃፋቸውን ይወቅሳሉ። ነገር ግን ኮለኔል አስጨናቂ ራሳቸው ስለ አሰብ እና ባድመ ጉዳይ በወቅቱ የነበራቸውን የግል አቋም ትንፍሽ አላሉም። እና ስለምን ሌላ ሰው መውቀስ አስፈለጋቸው?
#ጦርነቱ እንዲቆም ያደረጉ ግለሰቦች ኢህዴግ ውስጥ ነበሩ። ብለውን ጦርነቱ እንዲቆም መለስ ሳይሆን ያደረጉት ድርጅቱ ነው ባሉበት አንደበታቸው ከአይደር ትምህርት ቤት ጭፍጨፋ በኋላ ለኤርትራ ሽንጣቸውን ገትረው ተቆርቋሪ የሆኑ ሰዎች በድርጅቱ ውስጥ ነበሩ ያ ማለት ግን ድርጅቱ ለኤርትራ ይወግናል ማለት አይደለ ይሉናል። ግለሰብን ከድርጅት ለመነጠል ይሞክሩና ተንገዳግደው ድርጅቱና እና ግለሰቦችን ይቀላቅሉታል።
ሲጠቃለል
የአቶ መለስ ዜናዊን ስም መገንባትና ጦርነቱ በእኛ ድል አድራጊነት እንደተጠናቀቀ እንድናምን የተፃፈ ነው የሚመስለው።
እነዚህ ጉዳዮች በቀጣይ ፅሁፎቻቸው ግልፅ ያደርጉልናል ብለን ተስፋ እናደርጋለን። (የእኔ የአረዳድ ችግር ከሆነም አፉ ይሉኛል ብየ ተስፋ አደርጋለሁ)

ብሽቅ!!!!!


እኛ እርግማን ያለብን ይመለኛል። "መቼም ሰው አትሁኑ" የሚል ከባድ እርግማን፦እርግማኑ መሬት ጠብ የማይል ሰው የረገመን እርግማን። ወይ እንደ ናይጄሪያውያን ለምንፈልገው አገልግሎት "ሃላል" ገንዘብ አምጡ ተብለን በይፋ አልሰጠን ወይ ደግሞ "ኪራይ ሰብሳቢነትን ለመከላከል" እያልን መደስኮራችንን አልተውን አፋችን እና ልባችን ተለያይቶ እየኖርን ነው። ሰው የሚያወራውን የማይኖርባት፣ የተፃፈ የማይተገበርባት፣ ግብረ ገብነት ስሙ ሳይቀር የጠፋበት ዘመን (በእርጥ ሃገር ነው) ላይ ደርሰናል። ሰሞኑን የቀድሞ አስተማሪየን አግኝቼው ስለ ሃገራችን ጉዳይ የተወሰኑ ነገሮችን ስናወራ የነገረኝ ነገር በጣም አስደነገጠኝ። ሰውየው ከውጭ ሃገር በርካታ ገንዘብ ይዞ ይመጣል። አንድ ከተማ ውስጥ (ቦታውን እንተወው) ትምህርት ቤት ልስራና ወላጅ እና አሳዳጊ የሌላቸውን ህፃናት ማደሪያ እና ምግባቸውን ችየ ላስተምር ብሎ ጥያቄ ያቀርባል። (በእርግጥ ሰውየው የግለሰብ ቤት ተከራይቶ ይህንን እያደረገ ነው።ለማስፋፋት አስቦ ነው) "ቦታ እንዲፈቀድልህ ይህንን ያክል ገንዘብ አምጣ" ተባለ። እያዘነ "እኔ እኮ መተውም እችላለሁ" ነው ያለው። ይታያችሁ እንግዲህ ይሄ ሰው ልነግድብት ቦታ ስጡኝ አላለም፣ ፋብሪካ ልገንባም አላለም፣ የክፍያ ትምህርት ቤትም አይደለም ልገንባ ያለው። "የተቸገሩ የሚማሩበት የነፃ ትምህርት ቤት ልገንባ" ነው ያለው። ምን አይነት ጭንቅላት ያለው ሰው ነው ለዚህ ለበጎ አድራጎት ተግባር ገንዘብ ሰጠኝ የሚለው ልትሉ ትችላላችሁ። "የጭንቅላቱን አይነት እናንተ ስም አውጡለት" እንልና "ጭንቅላቱ ይፍረስ" ብለን ተራግመን እናልፋለን። (ከዚህ በላይ ምን አቅም አለንና?) አስተማሪየ ይህንን ሲነግረኝ እንባ እንባ እያለው ጭምር ነበር። እንኳን እሱ በማስተማር ተግባር ላይ እያለ እኔ ራሱ ይህንን ስሰማ የተሰማኝን መጥፎ ስሜት ብገልፀው አሸባሪ ተብየ ልፈረጅ እችላለሁ። በደማሚት ነበር ማፍረስ የምትሉት መስሪያ ቤት አጋጥሟችሁ ያውቅ የለ? ልክ እንደዚያ የገንዘብ ጠያቂውን ጭንቅላት ማፍረስ ነበር የታየኝ። ይሄንን ባደርግ በርካታ መማር ያልቻሉ ህፃናት አንድ ጋሬጣ ነቅየላቸው ትምህርት በነፃ ያገኛሉ፣የተመቻቸም ህይወት ይኖራሉ ብየም አሰብኩ። እንዲህ ያለ የቀን ጅብነት ከየት ወረስንው? እና ታዲያ ከዚህ በላይ እርግማን አለ?

CIA የሚባለው አሸባሪ

CIA የሚባለው አሸባሪ ይቅርታ የአሜሪካ የስለላ ተቋም አይነውሃቸው ያአላማሩትን ሃገሮች በዚህም በዚያም ብሎ የጦርነት አውድማ ያደርጋቸዋል። ዓለም ላይ የሚፈጠሩ ግጭቶች ሁሉ ላይ እጁ ቢኖርበትም ሌላው ቀርቶ ሊቢያን እና ኢራቅን እንኳ ትተን ሶርያን እናስባት። የሶሪያን ፕሬዝዳንት በሽር አላሳድን የኬሚካል የጦር መሳሪያ አለህ በሚል በኦባማ አስተዳደር ጥርስ ተነከሰበት። የሃገሪቱ በአሜሪካ ጥርስ ውስጥ መግባት የኬሚካል የጦር መሳሪያሽን አስወግጂ ከሚል በሉዓላዊት ሃገር ላይ በመግባት ወደ የሃገሪቱን ፕሬዝዳንት ከስልጣን ማውረድ ሃሳብ ተሸጋገረ። ይሄው ስድስት አመት ሆነ ሱሪያ ሰላም አጣች። የሚያማምሩ እና ጥንታዊ ከተሞቿ ወደሙ። የሃገሬው ህዝብ ግማሹ ተሰደደ። በሚሊየን የሚቆጠሩ ተገደሉ። ይህ የሆነው በበሽር አላሳድ ላይ እንዲነሱ የሰለጠኑ አማፅያን እና አይኤስም ጭምር ነው። አልጃዜራ እና ሌሎች የተወሰኑ የመገናኛ ብዙሃን አይኤስ የተባለውን አሸባሪ ቡድን የፈጠረችው እና ይልሰለጠነችው አሜሪካን ናት ስልጠናውን የወሰደው ደግሞ ቱርክ ውስጥ ነው ሲሉ አጋለጡ። ይህንን ጉዳይ ትራምፕ ለምርጫ ቅስቀሳቸውም ተጠቅመውበታል። አይኤስን የፈጠረው ኦባማ ራሱ ነው ብለው ቃል በቃል ተናግረዋል። በእርግጥ ምንም የማታውቀው ሃገራችን እንኳ የእነዚህ ሽብርተኛ ቡድኖች ሰላባ ስትሆን አሜሪካ ግን በፍፁም አልተነካችም። አሜሪካ ያልተነካችው ውለታን ላለመብላት ይመስላል። ዞር ትልና አሜሪካ ለሽብርተኞች ድጋፍ እያደረገች ሽብርተኝነትን እንዋጋ ትልሃለች። 6ዓመት ለዘለቀው የሶሪያ ጦርነት በአንድም በሌላ መልኩ አሜሪካ እሳት ስትቆሰቁስ እንደነበር ግልፅ ነው። ይባስ ብሎ አሜሪካ በሽብር ቡድኑ ላይ የአየር ጥቃት ፈፀምኩ ባለች ሰሞን ቡድኑ ተጨማሪ ይዞታዎችን በቁጥጥሩ ስር ሲያውል ነበር። አሜሪካ የአየር ጥቃት የምትለው ለአሸባሪ ቡድኑ መሳሪያ የማቀበል ተግባሯን ነው የሚሉም አሉ። 6ዓመት በፈጀው የእርስ በእርስ ጦርነት ለአሜሪካ በጦር መሳሪያ ሽያጭ ተጨማሪ ገቢ ሲሆናት አሸባሪ ቡድኑ ከሶሪያ ያገኘው የነበረውን ነዳጅ በቱርክ በኩል በውል አትርፋበታለች የሚሉም አሉ። ነዳጅ ትገዛለች የሄደባትን ብር የጦር መሳሪያ ሸጣ ትመልሰዋለች ነው ነገሩ። በአለም ላይ ተፅዕኖ ፈጣሪ የሚባሉት CNN እና BBC የመሳሰሉ መገናኛ ብዙሃን እንኳ ይቺን ትንፍሽ አይሉም። ይልቁንም የሶርያን ግጭት አድሏዊ በሆነ መልኩ ነበር ሲዘግቡት የነበረው።
ሰሞኑን ዶናልድ ትራም CIA ለሶሪያ አማፂዎች የሚሰጠውን ድጋፍ እንዲያቆም ወሰኑ የሚለው ዜና የእስካሁኑን ቁማር ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ ነው። አሜሪካ አማፂዎቹን ትደግፋለች የሚል ይፋዊ መረጃ ሳይወጣ ኖሮ የትራምፕ ውሳኔ ይህንን እውነት እርቃኑን ያስቀረ ነው። አማፂዎቹ አንድም አይ ኤስ ነው አንድም የኩርድ ታጣቂዎች አልያም ደግሞ የፒሽመርጋ ታጣቂዎች።(ኤራቅን ጨምሮ) እንደሚታወቀው በሶርያ ጉዳይ ሩስያ ገብታ ሶሪያን ከጡንቻ መፈተሻነት በተወሰነ መልኩ ታድጋታለች። አሜሪካንም ረገብ ያለችው ሩስያ ከአሳድ ጎን በመቆሟ ነው። በንፁሃን ሞት እና ስደት ላይ እቃ እቃ ስትጫዎት የነበረችውን አሜሪካ ይህ የሩስያ ከአሳድ ጎን መቆም እጅጉን አስቆጣት። ወደ ማዕቀብ መጣልም ወሰዳት። በዩክሬን ጉዳይ ንፋስ ገብቶበት የነበረው የሁለቱ ሃገራት ግንኙነት የባሰ ተሸረሸረ። ሩስያም በአቋማ ፀናች። በነገራችን ላይ የአሜሪካ ፍላጎት የሶርያውያንም ፍላጎት ቢሆን ኖሮ አሳድ ለአንድ ሳምንት እንኳ ስልጣን ላይ ባልቆየ ነበር። ስለዚህ ሰውየው የህዝብ ድጋፍ አለው ማለት ነው። አምባገነን መሪዎች ትንሽ ችግር ሲገጥማቸው ህዝቡ አባብሶ ገደል ይከታቸዋል እንጂ ህዝብ መቼም አይደብቃቸውም። ለማንኛውም ከእነ አሜሪካ በኩል ያለው የሃይል ሚዛንን ሊገዳደሩት የሚችሉት ሩስያና እና ቻይና ብቻ ናቸው። በቅርቡ የሰሜን ኮርያ ጉዳይ ደግሞ ሌላ አሰላለፍ አመጣ። አሜሪካ ሰሜን ኮርያ የኒውክለር መርሃ ግብሯን ካላቆመች ወታደራዊ እርምጃ ሁላ ልወስድ እችላለሁ አለች። ቻይና በጉዳዩ ዙሪያ ስትጠየቅ ችግሩን በሰላም እንዲፈታ የበኩሌን እወጣለሁ ብላ ወደ ንግዷ ተመለሰች። የቻይናን ድጋፍ በዚህ መልኩ ያጣችው አሜሪካ የሩስያን ከጎኗ መሰለፍ እንዴትም ልታገኝ አትችልም። በዩክሬን እና ሶርያ ጉዳይ ሆድ ተዋጥተው ትብብሩ እንዴት ሊታሰብ ይችላል? አሜሪካ በሌለ ነገር ኢራቅን ለአሸባሪ መፈንጫ እንዳደረገቻት ሁሉ ሰሜን ኮርያንም ልክ ማስገባት ትፈልግ ነበር። ያንን ለማድረግም የተለያዩ ማስፈራሪያዎችን አድርጋለች። አንዳንድ ባለሙያዎች የሰሜን ኮሪያን የሚሳኤል ጥቃት አሜሪካ የመመከት አቅም የላትም ሲሉ አሜሪካንን ሳያስደነግጣት አልቀረም። አሜሪካን ከደቡብ ኮርያ ጋር በጀመረችው የጦር ልምምድ እና "ወዳጄቼን ከሰሜን ኮርያ ጥቃት እከላከላለሁ" ዘመቻ ደቡብ ኮርያውያንን አስቆጣ። ደቡብ ኮርያውያን በሰሜን ኮርያ ልታስፈጁን ነወይ ብለው ተቃወሙት። ያለው አማራጭ ሁለቱን ኮርያዎች ነገሩን ወደ ሰላማዊ ትብብር አዙሩት ሆነ። አሜሪካ ባትፈራ ኖሮ ኢራቅ ውስጥ ገብታ የሉዓላዊቷን ኢራቅን መሪ በዚህ ሰዓት ሃገርክን ለቀህ ካልወጣህ ብላ ኤራቅን የጦር ቀጣና እንዳደረገቻት ሁሉ ሰሜን ኮርያ ውስጥም ገብታ ያንን ጎረምሳ መሪ በ24ሰዓት ካልወጣ አልያም በ48 ሰዓት የኒውክለር መረሃ ግብሩን ካላቆመ ብላ አስፈራርታ ሃገር ታፈርስ ነበር። ዛሬ የሰሜን ኮርያ ጡንቻ ይህንን እንድታደርግ አላስቻላትም። በሶሪያ ጉዳይ ወደ አዲሱ ፕሬዝዳንት ትራምፕ የተላለፈው ቅራኔ ሩስያን በሰሜን ኮርያ ጉዳይ ጥጓን እንድትይዝ አደረጋት። ይህንን የተረዱት ትራምፕ ጀርመን ከተካሄደው የቡድን 20 ሃገራት ስብሰባ ጎን ለጎን ከፑቲን ጋር ሲወያዩ ለሶርያ ሰላም እንሰራለን ሲሉ ተስማምተዋል። ወዲያው ነው ትራምፕ CIAን የአማፂዎችን መደገፍ እንዲያቆም የወሰኑት። የዓለም መገናኛ ብዙሃን ከውይይታቸው ውስጥ መርጠው ሲያራግቡት የነበረው የሩስያን በአሜሪካ ምርጫ ጣልቃ መግባት ጉዳይ ነበር። ከትራምፕ ጋር ቃለመጠይቅ ያደረጉ የአሜሪካ መገናኛ ብዙሀን ትራምፕን ወጥረው ይጠይቋቸው የነበረው ይህንን ነው። ስለምን ለሶርያ ሰላም ከሩስያ ጋር እንሰራለን አሉ የሚለውን ማንሳት አልፈለጉም? አንደኛ ይሄ ውሳኔ የአሜሪካንን ሽንፈት የሚያሳይ ነው። ሁለተኛ የሩስያን ተፅዕኖ ፈጣሪነት የሚያንፀባርቅ ነው። ትራምፕን የማይወዱት የአሜሪካ መገናኛ ብዙሃን እንኳ ሃገራቸው እጅ ሰጠች እንዳትባል ይመስላል ይቺን የዘለሏት። ትራምፕ ለሶርያ ሰላም እንሰራለን ሲሉ ጦርነቱ እንዲያበቃ ከሩስያ ጋር በሩስያ አካሄድ እንሰራለን ነው። ቻይንኛው ደግሞ በሩስያ መሸነፋችንንን አመነናል ነው። አሳድን ከስልጣን እስከ ማውረድ የደረሰ ሃሳብ በሩስያ ተበላ። ይህ የአሜሪካ ልስላሴ ወይም የፓለቲካ አክሮባት ልትጋፋት ያልቻለችውን ሰሜን ኮርያን ለመጣል ከሩስያ ጋር ስምም መሆንን ያለመ ይመስላል። ቻይናን እና ሩስያን ከጎኗ ካላሰለፈች ደግሞ ይሄ ነገር አይሳካም። ቻይና ደግሞ ለእንዲህ አይነት እብሪት የሚመስል አካሄድ እጇን አታስገባም። የቻይና ጨዋታ ከሌሎች ሃገራት ጋር ቢዝነስ እና ቢዝነስ ብቻ ነው። ሩስያም በሃሳብ ማፈንገጥ ከጀመረች ከርማለች። በሰሜን ኮርያ ጉዳይ ከአሜሪካ ጎን ትሰለፋለች ማለት ዘበት ነው። የወጋ ቢረሳ የተወጋ አይረሳ ነው ነገሩ። እንደ አሜሪካ ተንኮል ቢሆን ሩስያ በኢኮኖሜ ድቅቅ ብላ ነበር።ይቺን ረስቶ ማን ሞኝ አለ ከአሜሪካ ጎን የሚሰለፍ። የሆነው ሆኖ ፑቲን የአማሪካንን የጥቅም ፓለቲካ ተረድተው የሃይል ሚዘኑን በዚሁ እንዲቀጥል ካደረጉ የአሜሪካ በጥባጭነት ይገታና ዓለም ሰላም ወደ መሆን ታዘነብላለች። ሶርያና ኢራቅ ውስጥ የፈለፈለቻቸው አማፅዎች እና አሸባሪዎች እንዲጠፉ አሜሪካ እና የስለላ ተቋሟ ሃይ ባይ ያስፈልጋታል። ሃይ ባዩዋ ደግሞ ሩስያ ብቻ ናት። ብራቮ ፑቲን

የሰርግ ወሬዎች


እሁድ አለት (የአላዩ ገረመው እና የኤልሰቤጥ ሹምየ ሰርግ ነበር) ሙሺሪቷን ይዘን ከሙሽራው ቤተሰቦች ቤት ገጠር ሄድን። ከመኪና ወርደን 30 ደቂቃ ያክል የእግር መንገድ አለው። ማታ ጭቃ ስላልነበር ያለምንም ችግር ቢመሽም ገባን። ሰኞ እለት ስራ የነበረን ሰዎች 12 ሰዓት ተነስተን ወደ ደብረ ብረሃን ጉዞ ጀመርን። ሌሊቱን የዘነበው ዝናብ ጭቃ ሆኖ ጫማችንን እያስቀረ በጣም ተቸገርን። ያለን አማራጭ ጫማ ማውለቅ ሆነ። ጫማችንን አውልቀን ጉዞ ጀመርን። መሬቱ የጤፍ መሬት እና በጣም ለስላሳ ስለነበር ዋናውን መንገድ ትተን በታረሰው መሬት ላይ መሄድ ጀመርን። መሬቱን ስንረግጠው ፍራሽ የረግጥን ያክል ስምጥ ስምጥ ሲል በጣም ደስ ይላል። የታረሰውን መሬት ጨርሰን ፒስታው መንገድ ላይ ስንወጣ ጠጠሩን መርገጥ ተሳነኝ። ፒስታ መንገዱን አቋርጬ እግሬን ለመታጠብ ውሃ ወዳለበት ቦታ ለመሻገር ስሞክር ጠጠሩ ከቅዝቃዜው ጋር ውስጥ እግሬን ሲወጋኝ ህመሙ ጭንቅላቴ ድረስ ተሰማኝ። ሽምቅቅ ሽምቅቅ እያልኩ እንደምንም ተሻገርኩት። ጠጠሩ ከብርዱ ጋር አሠከረኝ ማለት ይቻላል። ቀጥታ አዕምሮየ ውስጥ የመጣልኝ ስለ ማዕከላዊ የወንጀል ምርመራ ያነበብኳቸው መፀሃፍት ናቸው። በባዶ እግር በብርጭቆ ስብርባሪ ላይ ይሄዱ እንደነበር ምስክረነታቸውን የሰጡ ሰዎች ስቃይ መጣብኝ። ለዚህ ጠጠር እንዲህ የሆንኩ እንደዚያ ያለ አደጋ ቢገጥመኝ ብየ አሰብኩት። ዘገነነኝ። የፓለቲካል ሳይንስ ትምህርት የመማር እቅዴን ወዲያውኑ ሰረዝኩት። welcome መሃይምነት።
ሌላ ወሬ
የመልሱ ዕለት ሴቷ ቤት ልንሄድ ስንነሳ በጉ የት እንደገባ ጠፋ። መኪና ላይ ተጭኖ ነበር አለን አንዱ ሚዜ። መኪናው ላይ የለም። እኔና ብረሃኑ ደብረ ብረሃን ስለነበርን መኪናው ላይ ጭነው ይምጡ አይምጡ የምናውቀው ነገር አልነበረም። በቃ በጉ ጠፋ። ሰዓቱ ከምሽቱ 1፡30 ሆኗል። 2፡00 ላይ ሙሺሪቷ ቤትሰቦች ቤት መድረስ አለብን። በግ ሳይያዝ እንዴት ይገባል? እኔ በጉ ከሌለ ታመምኩ ብየም ቢሆን እቀራታለሁ እንጂ ዳቦ ብቻ ይዘን እየጨፈርን አንገባም ብየ ለራሴ ቃል ገባሁ። በጉ ከመኪናው ላይ በረሮ ነው የጠፋው ተብሎ ተቀለደ። የሙዜውን ከርፋፋ በለው በአካፋ እንዲሉ 1ኛ እና 2ኛ ሚዜዎቹን በአካፋ ብጠርጋቸው ምንኛ ደስ ባለኝ። አጠብቂኝ ውስጥ ገባን። በ30 ደቂቃ ውስጥ ስልክ በዚየም በዚህም ስንደዋወል 3 ቦታ በግ ተገኘ። አንድ ቦታ ሄደን ገዝተን ስንመለስ በጉ ጠፋ በግ ፈልግልን ብየ የደወልኩለት ጓደኛየ መሲ ደወለልኝ። "የጠፋው በግ ምን አይነት ነው እኛ ሰፈር አንድ የተገኘ በግ አለ" አለን። ሚዜውን ደውየ
"ምን አይነት በግ ነው የጠፋው" ብለው እኛ ማግኘታችንን ስላወቀ ነው መሰለኝ
"እረስተንው ጭራሽ መቼ ገዛን!" አለንና አረፈው። ደግነቱ በጉን ስንገፍ ይህንን ከርፋፋ ሚዜ እጁን ቆረጥኩት እና ብድራችንን መለስን ተብሎ ታለፈ።
ሌላ ወሬ
የሙሽራው ቤተሰቦች ቤት የሄድን ቀን የእኛ ጭፈራ እና የአካባቢው ጭፈራ እንዴትም ሊገጥምልን አልችል አለ። የእኛ ጭፈራ አዲስ አበባ የሚዘወተረው እስክስታ አይነት ነው። እዚያ አካባቢ ያለው ደግሞ ጨፋሪዎቹ ጥንድ ጥንድ ይሆኑና ተራርቀው በእጃቸው በሃይል እያጨበጨቡ፣ ከእጃቸው ምት እኩል መሬቱን በአንድ እግራቸው እየመቱ እንዲሁም በእጃቸው በሚያጨበጭቡት እና መሬቱን በአንድ እግራቸው በሚመቱት እኩል "ህይይይ" ብለው እየጮሁ ነው የሚጨፍሩት። ጭፈራው በጣም ሃይል የሚፈልግ ነው። በአንድ ዙር ጭፈራ ፊታቸው ውሃ የፈሰሰበት እስኪመስል በላብ ይጠመቃል። እኔ ግን የጉሮሯቸውን ፅናት አደነኩኝ። ከደብረ ብረሃን የሄድንው ጦጣ ሆነን ቁጭ አልን። አንጉራጓሪው የሚደረድራቸው የወል ግጥሞች ግን እጅግ መሳጭ ናቸው።
"ስሙኒ ሰጥቻት ማታ ና ብላኝ
50ሳንቲም ሰጥቶ ከኋላ ቀማኝ" ይቺን ግጥም እዚያው ለግዜው የሰማኋት ግጥም ናት። ይሄ የሊብራሊዝም ቴዎሪ ነው። ብረሃኑ ድንቄ የምዕራባውያንን ፍልስፍና የእኛ ሃገር ቄሶች ቅኔ መሆኑን አስረግጠው የተናገሩበት አልቦ ዘመድ ትዝ አለኝ። ይሄ ግጥምም የእነ አሜሪካ የሊብራሊዝም ፍልስፍናና የዳርዊን አሸናፊው ይኖራል ቲዮሪ ነው።የሆነው ሆኖ ቁጭ ብለን የሃገሬውን ጭፈራ ስንኮመኩም አደርን ማለት ይቻላል። ከሚዜ ከርፋፋነት ወደ ሚዜ ጦጣ ሚዜነት

የምርጫው መንገድ


ባለፈው እንደባላባት አድርጎን የቤተመንግስት ጠጅ መጠጣት አለብን ብለን ወደ አንኮበር ቤተ መንግስት ጉዞ ጀመረን ነበር። ከደብረ ብረሃን አንኮበር ያለው ፒስታ መንገድ መኪናችንን እያርገፈገፈ ውልቅልቅ ሊያደርጋት ቃጣው። ለመዝናናት መሄዱ ቀርቶ መንገዱ ቀጥቅጦ ቀጥቅጦ መጉላላታችን ባሰ። ዝናብ ተጨመረበት። እስኪያባራ ብለን መኪናችንን ጥግ አስይዘን ቆምን። ዝናቡ አባርቶ ጉዞ ስንጀምር ከአንኮበር በኩል ህዝብ ጭኖ ለሚመጣ ተሽከርካሪ ቦታ እለቃለሁ ብሎ ዳር ሲይዝ የመኪናችን የቀኝ የኋላ እግር ጭቃ ውስጥ ሰመጠ። እግሩ ብቻውን እየተሽከረከረ ወደ ውስጥ እየጎደፈረ መንቀሳቀስ በአባቴም የለብኝ አለ። ይባስ ብሎ የፊት እግሩንም ጎትቶ ጭቃ ውስጥ ከተተው። ሹፌራችን "እኔ ድሮም መንገዱ የማይሆን መንገድ ነው ብየ ነበር" ምናምን እያለ ማለቃቀስ ጀመረ። በእርግጥ መንግዱ ውሃ ሽርሽሮት፣ አንዳንድ ቦታ ተቆፍሮ ውሃ ሞልቶት ያለ አስጠሊታ መንገድ ነው። ፀሃይ ወጥቶ አየሩ ሞቅ እስኪል ተቀመጥንና ሁለቱንም እግር በየተራ በክሪክ አንስተን ጠፍጣፋ ድንጋይ ላይ እንዲቀመጥ ካደረግን በኋላ ጭቃው ላይ ድንጋይ ስንደረድር ሁለት ገበሬዎች አገዙን። አንደኛው ገበሬ "አይ ይሄ የምርጫ መንገድ" ብሎ አዘነ። ሹፌራችን አሁንም ይነጫነጫል። ሰውየውን "የምርጫ መንገድ ምን ማለት ነው?" አልኩት። ፈገግ አለ።
"ይሄ መንገድ ምርጫ በመጣ ቁጥር ሊሰራ ነው ቲባል፣ ምርጫ በተቃረበ ቁጥር እገሌ ተሚባለው ኮንትራተር ጋራ መንገዱ ሊሰራ ስምምነት ተፈረመ ቲባል ይኸው ዛሬም አለ፣ እና እኛ ግራ ቢገባን ግዜና "የምርጫ መንገድ" አልነው። ለምርጫ መኧስኧሻ አድርገውት አረፉ። እንዳው ታዘበኝ ወንድሜ ተኧጣዩ ምርጫ ላይም ሊሰራ ነው ባይባል፥ ተምላሴ ነጭ ጠጉር ትነኧል። ቱ" አለኝ። ሹፌራችን ንጭንጩን ረስቶት
"ባለፈው አንዱ ጓደኛየ ምን ቢለኝ ጥሩ ነው" አለና ወሬ ሊያዳንቅ አፉን አሞጠሞጠ። ያ ነገረኛ ጓደኛችን
"ብዙ ገንዘብ እሰጥሃለሁ ቢልህ ጥሩ ነው" አለና ወሬ አቆረፈደበት። እኔ ነጭንጩን በዚያውም ይርሳው ብየ
"እሺ...." ብየ ወሬ አስጀመርኩት።
"በርካታ የመሰረት ድንጋይ ሊጣል ስንት አመት ቀረን? ብሎ ጠየቀኝ። ማለት የፈለገው ግራ ስለገባኝ ምን አይነት ጥያቄ ነው ብየ ተሳለኩበት። ባክህ ቀጣዩ ምርጫ መቼ ነው ለማለት ነው አለኝ። ይህንን ያነሳሁት የምርጫ መንገዱ ቢነሳ ግዜ ነው!"አለና አጫወተን።ወሬውን እህ ብለን ስለሰማንለትም ኩራት ቢጤ የተሰማው ይመስላል። ሁለቱም አርሶ አደሮች ጥርስ በጥርስ ሆኑ። ሁላችንም እየተሳሳቅን የጠጁን ፕሮግራም ሰርዘን ወደ ደብረ ብረሃን ለመመለስ ተስማምተን ተመለስን።እውነትም የምርጫ መንገድ!! እኔ እንኳ ፋና የነበርኩ ግዜ ሁለት ግዜ መንገዱ ሊሰራ ነው ብየ ዜና አንብቤያለሁ። ምነው ምላሴን በቆረጠው ነበር አይባል ነገር!? ቱ!!

Saturday 14 January 2017

ኮሌጅ እና ትዝታ
ትዝታ 2፦ ዘ ብሄረ ዩኒቨርሲቲ
@@@@@@@@@@@
ብሄር የሚለውን ቃል ለመጀመሪያ ጊዜ ያወኩት ዩኒቨርሲቲ ነው። ቀድሞ የማውቀው እከሌ ዘ ብሄረ ቡልጋ፣ እከሌ ዘ ብሄረ ዘጌ ምናምን በሚል ነው። ስለዚህ ብሄርን በሆነ ሰፈር ስም ነበር የማውቀው። ይህንን ነገር ፕሮፌሰር ፍቅሬ ቶሎሳ ፅፈውት በዚህ ዓመት አነበብኩት። ዩኒቨርሲቲ እየቆየሁ ስመጣ ብሄር ለሆነ ቋንቋ ተናጋሪ እንደተሰጠ ገባኝ። አማሪኛ ተናጋሪው አማራ፣ኦሮምኛ ተናጋሪው ኦሮሞ፣ ትግሪኛ ተናጋሪው ትግሬ፣ ጉራጊኛ ተናጋሪው ጉራጌ.... በሚል ተተረጎመ።እንዲህ ከሆነ ደግሞ ቋንቋ እንጂ ብሄር የሚባል ነገር የለም የሚል ድምዳሜ ውስጥ ገባሁ። በነገራችን ላይ አሁንም ቋንቋ እንጂ ብሄር የለም የሚል አስተሳሰብ ነው ያለኝ።
አማራ ልማት ማህበር፣ ኦሮሞ ልማት ማህበር፣ትግራይ ልማት ማህበር የሚሉ ማህበራት መጡና ገንዘብ አዋጡ መጣ። የአንደኛ ዓመት ተማሪዎች ወደ ግቢው ሲገቡ ተቋሙ ራሱ አቀባበል ያደርጋል። ከዚያ ዝቅ ሲል ደግሞ በትምህርት ክፍል ተማሪዎች "እንኳን ደህና መጣችሁ" ይባላሉ። ቆይቶ አስቀያሚው አቀባበል መጣ የአማራ ተወላጆች የኦሮሞ ተወላጆች የትግራይ ተወላጆ አቀባበል እየተባለ ከግቢው ውጪ ፕሮግራሞች መዘጋጀት ጀመሩ። ፑል ቤት እውላታለሁ እንጂ እንዲህ ያሉ ፕሮግራሞች ላይ መገኘት አይመቸኝም። ከቡዘና መልስ ያን ግዜ ብሄር የሚባለው የቋንቋ ክፍፍል ፍንትው አለልኝ። ትምህርት ቤት አይደል!!
የእኛ ክፍል በስልጣንም በነጥብ ሰቀላም ከፍተኛ ፊክክር የነበረበት ክፍል ነው። በየአመቱ መፈንቅለ ነጥብ ተደርጓል። ወዳጄ ምስክር አንደኛ አመት ላይ ሰቀለች።ሁለተኛ አመት ላይ ወዳጄ ያየሰው ካለምንም ደም መፍሰስ የተሳካ መፈንቅለ ነጥብ አድርጎ ሰቀለ። አንደኛ አመት እስጢፈኖስ የሚል ፊልም ሲሰሩ ስለነበር ለዚያ ነው የተዘረርኩት እያለ አሁን ድረስ ሲቆጭ ሰምቻለሁ። ያየሰው ግዕዝ የማይችል ነገር ግን እኔን ግዕዝ ያስኮረጀ ብቸኛ ሰው ነው።ካገኛችሁት ና "C"ህን ውሰድ በሉልኝ።ሶስተኛ ዓመት ላይ እኛም ፊልም ጀምረን የምማርበት ክፍል ሁላ ጠፍቶብኝ ነበር። ተመርቀን ከወጣን በኋላ ይህንን ፊልም ያየች የ8 ዓመት ልጅ ኮብል ስቶን ስጠርብ አይታ "ቱ ሞት ይሻላል። ፊልም እየሰራህ ድንጋይ ትጠርባለህ?" ብላኛለች። ከዚያ ወዲህ የካሜራ ፎብያ ተጠናወተኝ።
ዩኒቨርስቲያችን አሉኝ የሚላቸው 3 በጣም ዝነኛ ሰካራሞች ነበሩ። አንደኛው አንድ ቀን እኔ ፑል ቤት አምሽቼ እሱ ደግሞ ጠላ ቤት አምሽቶ ወደ ግቢ ሲገባ ተገናኘን። ግቢው ውስጥ ግንባታ ይካሄድ ስለነበር ትልቅ ጉድጓድ አለ። የተወሰነ ውሃም አለበት። ወደ ግቢ የሚያስገባውን ዋናውን መንገድ ትቼ ወጣ አልኩና ጉድጓዱን ዘልየ ተሻገርኩ። ልጁ በጣም ከመስከሩ የተነሳ (እፅም የወሰደ ይመስለኛል) እኔ ተንደርድሬ ዘልየ ስሻገር ከትትት ብሎ ሳቀብኝ እና
"ከዚያ ድረስ የተንደረደርክው ይቺን ለመዝለል ነው?" አለኝ። አሳሳቁ በጣም ያበሳጫል። እጁን ሆዱ ውስጥ ወሽቆ አጎንብሶ ነው የሚስቀው።ክክክክ..
"እኔማ ራመድ ብየ ነው የምሻገራት" ብሎ አንደኛው እግሩን አንስቶ ውሃው ውስጥ ቸርፏ አለበት። በውሃ እና ጭቃ በስብሶ እየተንዘረዘረ ወደ መኝታ ክፍሉ ገባ። ጠዋት ሱሪውን ሲያጥብ አገኘሁት።
አንደኛው ጓደኛችን ዶርሙ ውስጥ የሄድፎን ብጥስጣሽ ቀጣጥሎ ከመኝታው ዘንግ ጋር አገናኝቶ ሲደንስ ተገኝቶ "ፈታ" ተብሎ ተወራበት። ያንን ለምን እንዳደረገ እስከ አሁን ባይገባኝም ተመርቆ በመንግስት መስሪያ ቤት ኋላፊ ሆኗል። በነገራችን ላይ ሰቃይ የሚባል ተማሪ እና መንግስት ፈፅሞ እንዲታማበት የማይፈልግ ልጅ ነው። ዶርም ውስጥ የፖለቲካዊ ጉዳዮች ተነስተው ክርክር ከተደረገ እና ከተሸነፈ "እናታችሁን ልቀፍላችሁ" ብሎ ተነስቶ ይወጣል።
3ኛ አመት ተማሪ እያለን የውሃ ቀንን ድምቅ ባለ ሁኔታ አክብረን ማታ ረብሻ ተነሳ። ረብሻው የተነሳው ሃሙስ ቀን ስጋ ሳይቀርብ ቀርቶ ለእሁድ በመቀየሩ እና እሁድ እለትም ሳይቀርብ በመቅረቱ ነው። በጣም የሚያበሳጨው ግን ብጥብጡን ያስነሳው የውሃ ቀን መከበሩ ነው ተብሎ ተሳበበ። ጉዳዩ ደግሞ ቀጥታ ወደ እኛ ጋር ይመጣል- ወደ ጂሲ ኮሚቴው። በራሳቸው ጥፋት እንደሆነ ተማመንን። ማታ የመጀመሪያዎቹ አምስት ልጆች እስር ቤት ገባን።
እኔ እራት ለመብላት ከዶርም ወደ ውጭ ስወጣ ኮሊደር ላይ ተይዤ (ከነ ችጋሬ)
ከድር ከሽንት ቤት ሲወጣ ተይዞ
ባላቶሊ ከውጭ ወደ ግቢ ሲገባ በእንግሊዝኛ መልስ መልሶ
አንዱ ጩቤ ኪሱ ተገኝቶበት
አንዱ ተማሪ ያልሆነ የግቢ ሳር አጫጅ ግቢ ውስጥ ይዘውት (ምስኪን)
እኛ ከዚያ በኋላ የሆነውን ማየት አልቻልንም። እኛ ያለጥፋታቸው ነው የታሰሩት ተብለን ስንለቀቅ ባለጩቤው ቀረ። ስንወጣ ጓደኞቼ ወሬ አስወርተውብኝ ሲናፈስ አገኘሁ። አዲስ ሲገረፍ "ታንክ ዶርም ደብቄያለሁ" ብሎ አለ ብለው ተወራብኝ። ያሳለፍንው ግዜ እንዴት ደስስስ ይላል መሰላችሁ!! ...በናታችሁ ወደ ዩኒቨርሲቲ መልሱን
ኮሌጅ እና ትዝታ
ትዝታ 2፦ ዘ ብሄረ ዩኒቨርሲቲ

@@@@@@@@@@@
ብሄር የሚለውን ቃል ለመጀመሪያ ጊዜ ያወኩት ዩኒቨርሲቲ ነው። ቀድሞ የማውቀው እከሌ ዘ ብሄረ ቡልጋ፣ እከሌ ዘ ብሄረ ዘጌ ምናምን በሚል ነው። ስለዚህ ብሄርን በሆነ ሰፈር ስም ነበር የማውቀው። ይህንን ነገር ፕሮፌሰር ፍቅሬ ቶሎሳ ፅፈውት በዚህ ዓመት አነበብኩት። ዩኒቨርሲቲ እየቆየሁ ስመጣ ብሄር ለሆነ ቋንቋ ተናጋሪ እንደተሰጠ ገባኝ። አማሪኛ ተናጋሪው አማራ፣ኦሮምኛ ተናጋሪው ኦሮሞ፣ ትግሪኛ ተናጋሪው ትግሬ፣ ጉራጊኛ ተናጋሪው ጉራጌ.... በሚል ተተረጎመ።እንዲህ ከሆነ ደግሞ ቋንቋ እንጂ ብሄር የሚባል ነገር የለም የሚል ድምዳሜ ውስጥ ገባሁ። በነገራችን ላይ አሁንም ቋንቋ እንጂ ብሄር የለም የሚል አስተሳሰብ ነው ያለኝ።
አማራ ልማት ማህበር፣ ኦሮሞ ልማት ማህበር፣ትግራይ ልማት ማህበር የሚሉ ማህበራት መጡና ገንዘብ አዋጡ መጣ። የአንደኛ ዓመት ተማሪዎች ወደ ግቢው ሲገቡ ተቋሙ ራሱ አቀባበል ያደርጋል። ከዚያ ዝቅ ሲል ደግሞ በትምህርት ክፍል ተማሪዎች "እንኳን ደህና መጣችሁ" ይባላሉ። ቆይቶ አስቀያሚው አቀባበል መጣ የአማራ ተወላጆች የኦሮሞ ተወላጆች የትግራይ ተወላጆ አቀባበል እየተባለ ከግቢው ውጪ ፕሮግራሞች መዘጋጀት ጀመሩ። ፑል ቤት እውላታለሁ እንጂ እንዲህ ያሉ ፕሮግራሞች ላይ መገኘት አይመቸኝም። ከቡዘና መልስ ያን ግዜ ብሄር የሚባለው የቋንቋ ክፍፍል ፍንትው አለልኝ። ትምህርት ቤት አይደል!!
የእኛ ክፍል በስልጣንም በነጥብ ሰቀላም ከፍተኛ ፊክክር የነበረበት ክፍል ነው። በየአመቱ መፈንቅለ ነጥብ ተደርጓል። ወዳጄ ምስክር አንደኛ አመት ላይ ሰቀለች።ሁለተኛ አመት ላይ ወዳጄ ያየሰው ካለምንም ደም መፍሰስ የተሳካ መፈንቅለ ነጥብ አድርጎ ሰቀለ። አንደኛ አመት እስጢፈኖስ የሚል ፊልም ሲሰሩ ስለነበር ለዚያ ነው የተዘረርኩት እያለ አሁን ድረስ ሲቆጭ ሰምቻለሁ። ያየሰው ግዕዝ የማይችል ነገር ግን እኔን ግዕዝ ያስኮረጀ ብቸኛ ሰው ነው።ካገኛችሁት ና "C"ህን ውሰድ በሉልኝ።ሶስተኛ ዓመት ላይ እኛም ፊልም ጀምረን የምማርበት ክፍል ሁላ ጠፍቶብኝ ነበር። ተመርቀን ከወጣን በኋላ ይህንን ፊልም ያየች የ8 ዓመት ልጅ ኮብል ስቶን ስጠርብ አይታ "ቱ ሞት ይሻላል። ፊልም እየሰራህ ድንጋይ ትጠርባለህ?" ብላኛለች። ከዚያ ወዲህ የካሜራ ፎብያ ተጠናወተኝ።
ዩኒቨርስቲያችን አሉኝ የሚላቸው 3 በጣም ዝነኛ ሰካራሞች ነበሩ። አንደኛው አንድ ቀን እኔ ፑል ቤት አምሽቼ እሱ ደግሞ ጠላ ቤት አምሽቶ ወደ ግቢ ሲገባ ተገናኘን። ግቢው ውስጥ ግንባታ ይካሄድ ስለነበር ትልቅ ጉድጓድ አለ። የተወሰነ ውሃም አለበት። ወደ ግቢ የሚያስገባውን ዋናውን መንገድ ትቼ ወጣ አልኩና ጉድጓዱን ዘልየ ተሻገርኩ። ልጁ በጣም ከመስከሩ የተነሳ (እፅም የወሰደ ይመስለኛል) እኔ ተንደርድሬ ዘልየ ስሻገር ከትትት ብሎ ሳቀብኝ እና
"ከዚያ ድረስ የተንደረደርክው ይቺን ለመዝለል ነው?" አለኝ። አሳሳቁ በጣም ያበሳጫል። እጁን ሆዱ ውስጥ ወሽቆ አጎንብሶ ነው የሚስቀው።ክክክክ..
"እኔማ ራመድ ብየ ነው የምሻገራት" ብሎ አንደኛው እግሩን አንስቶ ውሃው ውስጥ ቸርፏ አለበት። በውሃ እና ጭቃ በስብሶ እየተንዘረዘረ ወደ መኝታ ክፍሉ ገባ። ጠዋት ሱሪውን ሲያጥብ አገኘሁት።
አንደኛው ጓደኛችን ዶርሙ ውስጥ የሄድፎን ብጥስጣሽ ቀጣጥሎ ከመኝታው ዘንግ ጋር አገናኝቶ ሲደንስ ተገኝቶ "ፈታ" ተብሎ ተወራበት። ያንን ለምን እንዳደረገ እስከ አሁን ባይገባኝም ተመርቆ በመንግስት መስሪያ ቤት ኋላፊ ሆኗል። በነገራችን ላይ ሰቃይ የሚባል ተማሪ እና መንግስት ፈፅሞ እንዲታማበት የማይፈልግ ልጅ ነው። ዶርም ውስጥ የፖለቲካዊ ጉዳዮች ተነስተው ክርክር ከተደረገ እና ከተሸነፈ "እናታችሁን ልቀፍላችሁ" ብሎ ተነስቶ ይወጣል።
3ኛ አመት ተማሪ እያለን የውሃ ቀንን ድምቅ ባለ ሁኔታ አክብረን ማታ ረብሻ ተነሳ። ረብሻው የተነሳው ሃሙስ ቀን ስጋ ሳይቀርብ ቀርቶ ለእሁድ በመቀየሩ እና እሁድ እለትም ሳይቀርብ በመቅረቱ ነው። በጣም የሚያበሳጨው ግን ብጥብጡን ያስነሳው የውሃ ቀን መከበሩ ነው ተብሎ ተሳበበ። ጉዳዩ ደግሞ ቀጥታ ወደ እኛ ጋር ይመጣል- ወደ ጂሲ ኮሚቴው። በራሳቸው ጥፋት እንደሆነ ተማመንን። ማታ የመጀመሪያዎቹ አምስት ልጆች እስር ቤት ገባን።
እኔ እራት ለመብላት ከዶርም ወደ ውጭ ስወጣ ኮሊደር ላይ ተይዤ (ከነ ችጋሬ)
ከድር ከሽንት ቤት ሲወጣ ተይዞ
ባላቶሊ ከውጭ ወደ ግቢ ሲገባ በእንግሊዝኛ መልስ መልሶ
አንዱ ጩቤ ኪሱ ተገኝቶበት
አንዱ ተማሪ ያልሆነ የግቢ ሳር አጫጅ ግቢ ውስጥ ይዘውት (ምስኪን)
እኛ ከዚያ በኋላ የሆነውን ማየት አልቻልንም። እኛ ያለጥፋታቸው ነው የታሰሩት ተብለን ስንለቀቅ ባለጩቤው ቀረ። ስንወጣ ጓደኞቼ ወሬ አስወርተውብኝ ሲናፈስ አገኘሁ። አዲስ ሲገረፍ "ታንክ ዶርም ደብቄያለሁ" ብሎ አለ ብለው ተወራብኝ። ያሳለፍንው ግዜ እንዴት ደስስስ ይላል መሰላችሁ!! ...በናታችሁ ወደ ዩኒቨርሲቲ መልሱን
የኮሌጅ ትዝታ
ግልባጭ ለደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች

((((((((((((((((((((((((((((((((())))))))))))))))))))))))))))
ትዝታ 1, ኮሌጅ እና ፖለቲካ
@@@@@@@@@
"የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች" እንደተባልን የመጀመሪያው ምርጫ ትምህርት ክፍል መረጣ ነው። የእኛ የመጀመሪያ ምርጫ የነበረው ግን "ዱርየ እንሁን ወይስ አንሁን" የሚለው ነው። በአብላጫ ድምፅ ዱርየ እንድንሆን ተወሰነ። ነብር የገደልን ይመስል ፀጉር አሳደግን፣እንደ ጀግና ጆሮ ጉትቻ አደረጉ (እኔ ጆሮ መበሳት ስለማይመቸኝ አልተበሳሁም) ሱሪያችንን ዝቅ አደረግን፤ የግቢውን አቧራ ለመከላከል በሚል ሱሪያችንን ከታች አጥፈን በብር ማሰሪያ ላስቲክ አሠርን። ቆይቶ ላስቲኩ አልበረክት ቢለን በኮንዶም ጫፍ ማሰር ጀመርን። ከተማ ገብተን በ2 ብር 8 ሙዝ 4ቱን በብር 4ቱን አጭበርብረን ገዝተን መብላት ሙዳችን ሆነ። ዱርየዎች ሆንን። ፑል ቤት 1ሰው ቁማር ለመብላት 3 ሰው አሰለፍን። የግቢ በር እየተዘጋብን ከጅብ ጋር እየታገልን በጫካ መግባት ጀመርን። (የእኛ ግቢ ከአንድ በኩል ሙሉ ለሙሉ ጫካ ስለነበር አጥር አልነበረውም። ስለዚህ ፈሪ ካልሆንክ በቀር በር ተዘግቶብህ ውጭ አታድርም) እንዲህ እንዲህ እያልን የመጀመሪያው መንፈቅ አመት ተጠናቀቀ። የዱርየው ቡድን አብዛኛው ሰው በውጤት ሰቃይ ሆኖ ተገኘ።'እነዚህ ልጆች ሰው እያዘናጉ' ተባለ። እኛ ክፍል ደንግጦ ነው መሰለኝ የሰቀለብን Miskir Agegnehu ነው። መጨረሻ ላይ ግን Yayesew Shimelis ጠቀለለን። ቆይቶ እኔ እና ምስክር ከአንደኛው መምህር ጋር ተጣላን። ምስክርን ሽማግሌው በእርግጫ ሲመቱት እኔ ፀጉርህን ሳትቆረጥ እንዳትገባ ተባልኩ። የመምህሩ እግር አነሳስ አሁንም አይኔ ላይ አለ። ከክፍል መቅረት የማይታሰብ ስለነበር እኔ በማግስቱ ፀጉሬን ተቆርጨ ገባሁ። "ቲቸር ይሄው ተቆረጨ መጣሁ" ብላቸው "እኔ እኮ ትንሽ አጠር አድርገው ነበር እንጂ እንዲህ ተቆረጠው አላልኩም" ብለው አስፈቱኝ (አናደዱኝ)። ነፍስ ይማር ድሬር!! በአመቱ መጨረሻ መምህር ስንገመግም መምህሩ "በእርግጫ ተማሪ ይማታሉ" ሲባሉ "እኔ አላስታውስም" አሉ። የአራዳ ልጅ!! እንዲህ እንዲህ እያለ የእኛ ክፍል አንገቱን ቀና ማድረግ ጀመረ። የፓለቲካው ጉዳይም ተንቀሳቀቀሰ። Z ቀንደኛ የኢህአዴግ ተቃዋሚ ነገር ግን ለብዓዴን አባል የሚመለምል ልጅ ነበር። እኔንም አንድ ግዜ "ለምን አባል አትሆንም ስትመረቅ ስራ ታገኛለህ" ብሎኝ ነበር ። "አንተ ስለምትቀጠር በጓደኝነት ታስቀጥረኛለህ" ብየው ተለያየን። ከእኛ ክፍል 2 ልጆች ብቻ አባል ያልሆንን ስንገኝ ከተለያየ ትምህርት ክፍል የተሰባሰበው የዱርየው ቡድንም እንዲሁ አንዱም አባልነት ውስጥ አልነበሩም። መጨረሻ ላይ አንዱ የክፍል ጓደኛየ "ምን ቸገረህ ዝም ብለህ አባል ሁን" ብሎኝ ስብሰባ እንድገኝ አደረገኝ። ዩኒቨርሲቲው ግቢ ውስጥ የፖለቲካ ስብሰባ ማድረግ ስለማይቻል ጫካ ውስጥ ለመጀመሪያ ግዜ ተሰበሰብኩ። ግምገማ ተጀመረ።
"አንተ በግ ተራ መቆም ታበዛለህ፣ እገሌ ከእንትና ጋር ተጣልተዋል እና የተጣሉት ደግሞ በዚህ ምክንያት ነው፤ አንተ መንገድ ላይ ሰላም አትለንም" ምናምን የሚሉ የግምገማ ሃሳቦች መምጣት ሲጀምሩ ስብሰባውን አቋርጬ በዚያው ጫካ ገባሁ።(ጫካ ስል ደግሞ ሌላ እንዳይመሥላችሁ። ከጫካው ውስጥ ኳስ የምንጫወትበት ሜዳ ስላለ ነው) ከዚያ ወዲህ የማንኛውም የፖለቲካ ድርጅት አባል ሳልሆን እስከ አሁን አለሁ። 2ኛ እና 3ኛ ዓመት ላይ ክበባት ውስጥ መሳተፍ ጀመርኩ። ቆይቶ የመዝናኛና ስነ-ፅሁፍ ክበብ ምክትል ፕሬዝዳንትነት ስልጣን ተሰጠኝ።( ሃሃ ም/ፕሬዝዳንት!!) የግቢው ስልጣን የሃይል ሚዛን ወደ እኛ ክፍል አመራ። የተማሪዎች ህብረት ምክትል ፕሬዝዳንት፣የጂሲ ኮሚቴ ምክትል ፕሬዝዳንት፣የፀረ ኤድስ ክበብ ምክትል ፕሬዝዳንት፣የመዝናኛና ስነ-ፅሁፍ ክበብ ምክትል ፕሬዝዳንት፣ የጂሲ ኮሚቴ መዝናኛና ስነፅሁፍ ክፍል ተጠሪ የሚባሉት ስልጣኖች ተጠቅልለው እኛ ክፍል መጡ።ተሿሚዎች Gtnet Asrat Yayesew Shimelis Gashaw Eshetu አዲስ መኮንን :: እኔ በመዝናኛና ስነ - ፅሁፍ በምክትል ፕሬዝዳንትነት ማዕረግ የጂሲ ኮሚቴውን የመዝናኛ ክፍል ተጠሪነት ደርቤ ያዝኩ። ስልጣን ሲመጣ እንዲህ ነው!! ይሄ የሆነው ግን ዱርየነቴን ከተውኩ በኋላ ነው።በእነዚህ አይነት የስልጣን ክፍፍል የሃይል ሚዛኑ ከአንድ ክፍል ወጥቶ ወደ ሸዋ አደላ ተብሎም ብዙ ታማን። የፖለቲካው የሃይል ሚዛን ደግሞ ወደ ጎጃም እና ጎንደር አምርቷል ተባለ። የብአዴንን አባልነት አብዛኛውን ስልጣን እነሱ ይዘውታል ተብሎ ቅሬታ የቀረበበት የምስራቅ ጎጃም ዞን የብአዴን ፅህፈት ቤት ኋላፊ መሰለኝ
"የሸዋ ሰው አትንኩኝ አልነካችሁም ፤ አትድረሱብኝ አልደርስባችሁም ነው። እና እኛ ምን እናድርጋችሁ" አለን ብለው ሢያስቁን ነበር።
እኔ በስልጣን ዘመኔ (ከ2003 -2004) የበደልኩት ወይም የጨቆንኩት ሰው ባይኖርም የስነ ፅሁፍ ምሽት ስናዘጋጅ ተማሪ እየበዛ በመምጣቱ አንድ ቀን አዳራሽ ሞልቶብን በር እንዲዘጋ እና ተማሪ እንዳይገባ አዝዤ ነበር። ያን ግዜ "ተማሪዎችን ስነ-ፅሁፍ ምሽት ላይ ገንዘብ እያስከፈለ አስገባ" ተብሎ ተወራብኝ። የስለላ መረቤን ዘርግቼ ጉዳዩን ሳጣራ በር ላይ የነበሩ ልጆች የተማሪውን መብዛት አይተው የተወሰኑ ተማሪዎችን እያስከፈሉ እንዳስገቧቸው ደረስኩበት። ልጆቹን አድሳለሁ ስል እኔም ሳላድሳቸው እነሱም ለእድሳት ሳይበቁ ተመርቀን ወጣን። ይብላኝ ለቀጠራቸው ተቋም!!
በስልጣን ዘመኔ የሚቆጨኝ ግን የምረቃ መፅሄታችን ላይ የወጣው የስነ-ፅሁፍ ስራ ነው። በጣም ጥሩ ጥሩ የስነ-ፅሁፍ ስራዎችን ገምግመን ካፀደቅን በኋላ ሁለቱን ልጆች ለአርትኦት ስራ አዲስ አበባ ልከናቸው አንደኛው ለፍቅረኛው የፃፈላትን ደብዳቤ የሚመስል ግጥም አትሞበት መጣ።
በስተመጨረሻ ከእኛ ክፍል መንግስትን ክፉኛ ይቃወም የነበረ ልጅ ሃገሩ ገብቶ የወጣት ሊግ ሰብሳቢ ሆኖ አግኚቼው "ምነው?" ብለው
"አብዮታዊ ዲሞክራሲ ተጠምቄያለሁ"ብሎ አለኝ። ምስኪን Z ደግሞ ለብዓዴን አባል ስትመለምል ከርማ መጨረሻ ላይ ሰክሮ ነው አሉ "የወያኔን ዲግሪ ማየት አልፈልግም" ብሎ ግዜያዊ የዲግሪ ወረቀቱን መንገድ ላይ እንደቀደደው ሰምቻለሁ)።
ክንፍፍፍፍ ያለ ፍቅር ያየዘኝም ያን ግዜ ነበር።
"ያሳለፍነው ግዜ ደስታን ያየንበት
ተመልሶ ቢገኝ አሁን ምን አለበት" አለ ጥልሽ!!
የሩስያ እና የአሜሪካ ፍጥጫ
@@@@@@@@@@@
ምንም እንኳ የእነዚህ የሁለት ጡንቻማ ሃገራት መማዘዝ ቆይቶ እኛን የመሳሰሉ ድሃ ሃገራትን ቢደፈጥጥም ፍጥጫቸው ያጓጓል። አብዛኛው አሜሪካዊ የሩስያ መግነን የሃገራቸውን ሃያልነት ይውጣል ከሚል ፍራቻ ይመስላል ቁጭት ውስጥ ናቸው። በተለይ ደግሞ ለአሜሪካ ፕሬዝዳንትነት ስትጠበቅ የነበረችው ሂላሪ ባልተጠበቀ ሁኔታ በትራምፕ መሸነፏ እና የትራምፕ ማሸነፍ ደግሞ የሩስያ እጅ ነበረበት መባሉ የሩስያን እጀ ረጅምነት እና የአሜሪካንን ዝርክርክነት ያሳየ በመሆኑ ብዙዎችን አበሳጭቷል። ሩስያ የእውነት ይህንን አድርጋ ከሆነ እውነትም ተፅዕኖ እየፈጠረች ነው። ትራምፕ እንደሚሉት እና ሲ አይ ኤ እና የአሜሪካ መገናኛ ብዙሃን በሬ ወለደ እያሉ አሜሪካንን እያሳሳቱ ነው የሚሉት ነገር ሚዛን የሚደፋ ከሆነ የሂላሪ አለመመረጥ ሄዶ ሄዶ አሜሪካ ህዝብ ላይ ያርፋል። ምክንያቱም የምርጫ ማሽኑ ካልተጠለፈ እና ትራምፕ በትክክለኛ ምርጫ ከሆነ ያሸነፉት ትራምፕ በቅስቀሳቸው ወቅት የተከተሉት አነጋጋሪ የምርጫ ቅስቀሳዎች አሜሪካውያን ልብ ውስጥ ገብተው ነበር ማለት ነው። ስለዚህ የአሜሪካ ህዝብ በሌሎች ሃገራት ሰዎች በገዛ ሃገራችን በኢኮኖሚ ተበለጥን እና ሌሎችም የሃይማኖት፣የዘር እና የመሳሰሉት ጥላቻዎች ሰርፀው ገብተውበታል ማለት ነው። ያ ደግሞ አሜሪካን ለዘመናት ገነባሁት የምትለው ዲሞክራሲን ገደል የሚከትተው ይመስላል። የሆነው ሆኖ ትራምፕ አሸንፈዋል። ለትራምፕ መመረጥ የሩስያ እጅ መኖሩን ትልቅ መተማመን አለኝ ባለው ሲ አይ ኤ መሰረት የዩ ኤስ ሲናተሮች እንደ ሃገር በሩስያ ላይ እንደ ግለሰብ ደግሞ በፑቲን ላይ ማዕቀብ መጣል አለበት እያሉ ያዙን ልቀቁን እያሉ ነው። ሩስያ በክሬምያ ጉዳይ የተጠለባት ማዕቀብ ሳይነሳ ድጋሚ ሌላ ማዕቀብ የሚጣልባት ከሆነ ካለምንም ጥርጥር መጎዳቷ አይቀርም። መዘዙ ግን ለሌሎችም ይተርፋል።2014ላይ የአውሮፓ ህብረት ማዕቀብ የጣለባት ግዜ ከዚያ አካባቢ የሚመረተውን የግብርና ምርጥ ወደ ሃገር ውስጥ አላስገባም ብላ በርካታ አምራቾችን ለኪሳራ ዳርጋለች። እንደሚታወቀው ሩስያ ከፍተኛ መጠን ያለው የግብርና ምርትን ወደ ሃገሯ ታሰገባለች። በማዕቀቡ ምክንያት አፃፋ ለመመለስ ምርት ማስገባቱን ስታቆም ሳምንት ባለሞላ ግዜ ውስጥ የምዕራቡ ዓለም አምራቾች ተንጫጩ። "እሾኽን በእሾህ" ማለት ይሄ ነው። የአሜሪካንን ጡጫ በዚህ ምድር ላይ ካለ ሩስያ የሚቋቋመው የለም። ለዚህም ነው አሜሪካ ሩስያን የሾርኒ የምትመለከታት። ለማንኛውም ስልጣናቸውን በቅርቡ ለትራምፕ የሚያስረክቡት ኦባማ ሊተላለፍ የሚችለውን ውሳኔ ይፋ ያደርጋሉ ተብሎ እየተጠበቀ ነው። ውሳኔው ምንም ይሁን ምን "አሜሪካ በምትወስነው ውሳኔ ምላሹን ወደያው ታገኘዋለች" እያሉ ነው የሩስያ ባለስልጣናት። በትራምፕ ማሸነፍ የሚብሰለሰውለው ብዙሃን መገናኛው እና ሲ አይ ኤ ጉዳዩን እያራገበ አሸናፊውን ፕሬዝዳንት አጣብቂኝ ውስጥ ሊከትቱት ነው። ከሩስያ ጋር በጋራ እንሰራለን ያሉት ትራምፕ በሩስያ ላይ ሊወሰድ የታሰበው እርምጃ የተሳሳተ እሳቤ ነው ብለው እየተከራከሩ ቢሆንም ጉዳዩ ገፍቶ ሩስያ ላይ ማዕቀብ ተጥሎ ስልጣናቸውን ከተረከቡ ማጣፊያው ሊያጥራቸው ይችላል። እውነትም በሩስያ እገዛ ከሆነ ወደ ስልጣን የመጡት ደግሞ ይቺን ባለውለታ ሃገር እንዴት አድርገው ያስቀይሟታል? አሜሪካ ከአንጀት ይሁን ከአንገት እንጃ እንጂ በእስራኤል የሰፈራ ፕሮግራም ዙሪያ ከእስራኤል ጋር እስከዚህም የመሆን አዝማሚያ እየታየባት ነው። ወዲያ ደግሞ ቻይና የታይዋይን ጉዳይ በጥንቃቄ ልታየው ይገባል እየተባለች ነው። ስልጣን የሚለቀው የኦባማ አስተዳደር ለትራምፕ ትልቅ የቤት ስራ እያዘጋጁላቸው ነው። ትረምፕ አንድ ግዜ ጡርምባውን ከነፉት "ነፍስ ይማር አሜሪካ" የሚል ድምፅ የሚያወጣ ይመስለኛል።
የሩስያ እና የአሜሪካ ፍጥጫ
@@@@@@@@@@@
ምንም እንኳ የእነዚህ የሁለት ጡንቻማ ሃገራት መማዘዝ ቆይቶ እኛን የመሳሰሉ ድሃ ሃገራትን ቢደፈጥጥም ፍጥጫቸው ያጓጓል። አብዛኛው አሜሪካዊ የሩስያ መግነን የሃገራቸውን ሃያልነት ይውጣል ከሚል ፍራቻ ይመስላል ቁጭት ውስጥ ናቸው። በተለይ ደግሞ ለአሜሪካ ፕሬዝዳንትነት ስትጠበቅ የነበረችው ሂላሪ ባልተጠበቀ ሁኔታ በትራምፕ መሸነፏ እና የትራምፕ ማሸነፍ ደግሞ የሩስያ እጅ ነበረበት መባሉ የሩስያን እጀ ረጅምነት እና የአሜሪካንን ዝርክርክነት ያሳየ በመሆኑ ብዙዎችን አበሳጭቷል። ሩስያ የእውነት ይህንን አድርጋ ከሆነ እውነትም ተፅዕኖ እየፈጠረች ነው። ትራምፕ እንደሚሉት እና ሲ አይ ኤ እና የአሜሪካ መገናኛ ብዙሃን በሬ ወለደ እያሉ አሜሪካንን እያሳሳቱ ነው የሚሉት ነገር ሚዛን የሚደፋ ከሆነ የሂላሪ አለመመረጥ ሄዶ ሄዶ አሜሪካ ህዝብ ላይ ያርፋል። ምክንያቱም የምርጫ ማሽኑ ካልተጠለፈ እና ትራምፕ በትክክለኛ ምርጫ ከሆነ ያሸነፉት ትራምፕ በቅስቀሳቸው ወቅት የተከተሉት አነጋጋሪ የምርጫ ቅስቀሳዎች አሜሪካውያን ልብ ውስጥ ገብተው ነበር ማለት ነው። ስለዚህ የአሜሪካ ህዝብ በሌሎች ሃገራት ሰዎች በገዛ ሃገራችን በኢኮኖሚ ተበለጥን እና ሌሎችም የሃይማኖት፣የዘር እና የመሳሰሉት ጥላቻዎች ሰርፀው ገብተውበታል ማለት ነው። ያ ደግሞ አሜሪካን ለዘመናት ገነባሁት የምትለው ዲሞክራሲን ገደል የሚከትተው ይመስላል። የሆነው ሆኖ ትራምፕ አሸንፈዋል። ለትራምፕ መመረጥ የሩስያ እጅ መኖሩን ትልቅ መተማመን አለኝ ባለው ሲ አይ ኤ መሰረት የዩ ኤስ ሲናተሮች እንደ ሃገር በሩስያ ላይ እንደ ግለሰብ ደግሞ በፑቲን ላይ ማዕቀብ መጣል አለበት እያሉ ያዙን ልቀቁን እያሉ ነው። ሩስያ በክሬምያ ጉዳይ የተጠለባት ማዕቀብ ሳይነሳ ድጋሚ ሌላ ማዕቀብ የሚጣልባት ከሆነ ካለምንም ጥርጥር መጎዳቷ አይቀርም። መዘዙ ግን ለሌሎችም ይተርፋል።2014ላይ የአውሮፓ ህብረት ማዕቀብ የጣለባት ግዜ ከዚያ አካባቢ የሚመረተውን የግብርና ምርጥ ወደ ሃገር ውስጥ አላስገባም ብላ በርካታ አምራቾችን ለኪሳራ ዳርጋለች። እንደሚታወቀው ሩስያ ከፍተኛ መጠን ያለው የግብርና ምርትን ወደ ሃገሯ ታሰገባለች። በማዕቀቡ ምክንያት አፃፋ ለመመለስ ምርት ማስገባቱን ስታቆም ሳምንት ባለሞላ ግዜ ውስጥ የምዕራቡ ዓለም አምራቾች ተንጫጩ። "እሾኽን በእሾህ" ማለት ይሄ ነው። የአሜሪካንን ጡጫ በዚህ ምድር ላይ ካለ ሩስያ የሚቋቋመው የለም። ለዚህም ነው አሜሪካ ሩስያን የሾርኒ የምትመለከታት። ለማንኛውም ስልጣናቸውን በቅርቡ ለትራምፕ የሚያስረክቡት ኦባማ ሊተላለፍ የሚችለውን ውሳኔ ይፋ ያደርጋሉ ተብሎ እየተጠበቀ ነው። ውሳኔው ምንም ይሁን ምን "አሜሪካ በምትወስነው ውሳኔ ምላሹን ወደያው ታገኘዋለች" እያሉ ነው የሩስያ ባለስልጣናት። በትራምፕ ማሸነፍ የሚብሰለሰውለው ብዙሃን መገናኛው እና ሲ አይ ኤ ጉዳዩን እያራገበ አሸናፊውን ፕሬዝዳንት አጣብቂኝ ውስጥ ሊከትቱት ነው። ከሩስያ ጋር በጋራ እንሰራለን ያሉት ትራምፕ በሩስያ ላይ ሊወሰድ የታሰበው እርምጃ የተሳሳተ እሳቤ ነው ብለው እየተከራከሩ ቢሆንም ጉዳዩ ገፍቶ ሩስያ ላይ ማዕቀብ ተጥሎ ስልጣናቸውን ከተረከቡ ማጣፊያው ሊያጥራቸው ይችላል። እውነትም በሩስያ እገዛ ከሆነ ወደ ስልጣን የመጡት ደግሞ ይቺን ባለውለታ ሃገር እንዴት አድርገው ያስቀይሟታል? አሜሪካ ከአንጀት ይሁን ከአንገት እንጃ እንጂ በእስራኤል የሰፈራ ፕሮግራም ዙሪያ ከእስራኤል ጋር እስከዚህም የመሆን አዝማሚያ እየታየባት ነው። ወዲያ ደግሞ ቻይና የታይዋይን ጉዳይ በጥንቃቄ ልታየው ይገባል እየተባለች ነው። ስልጣን የሚለቀው የኦባማ አስተዳደር ለትራምፕ ትልቅ የቤት ስራ እያዘጋጁላቸው ነው። ትረምፕ አንድ ግዜ ጡርምባውን ከነፉት "ነፍስ ይማር አሜሪካ" የሚል ድምፅ የሚያወጣ ይመስለኛል።
ዘረኝነት የፍቺ ምክንያት ሲሆን
@@@@@@@@@@@
እኔ የምለው በዓሉ እንዴት ነበር? ክርስቶስ ለእኛ ፍቅርን ሊያስተምር የተወለደበትን ቀን እያከበርን ነው። የዘንድሮው የልደት በዓል ከአምናው የሚለየው ዘንድሮ ጥላቻን እየዘሩ ላስቸገሩን አሁንም ፍቅርን እየተማርን የምናስተምርበት መሆኑ ነው። ልበል እንዴ? ለነገሩ አልኩ። ፍቅርን ፍቅር ከሚያውቁ ሁሉ እንማራለን። በአምሳሉ የፈጠረውን ሰው ሁሉ እንወዳለን። መውደድ ስል ምን ትዝ አለኝ መሰላችሁ ፍቅር፤ ፍቅር ስል ደግሞ ትዳር። እናላችሁ በዚህ በልደት በዓል ረፋድ ላይ ከቤት ወደ ሡቅ ስወጣ ከኋላየ አንድ ወጣት ስልክ እያወራ ይከተለኛል። በዓል እንደመሆኑ ብዙዎቹ ሱቆች ተዘግተው ጎዳናው እረጭ ብሏል። እናም ልጁ የሚያወራው በሙሉ ይሰማኛል። ከንግግሩ ከትዳር ጓደኛው ጋር እንደተለያዩ ተረዳሁ።
"እየውልህ እኔ እኮ ልጅቷን ሳልወዳት ቀርቼ አይደለም። እወዳታለሁ። እንደምትወደኝም አምናለሁ"
ይልና የዚያኛውን ስልክ ደግሞ ይሰማል። ያኛው ከሚስትህ ጋር ታረቁ እያለ እየመከረው እንደሆነ ገባኝ። በዚህ በዓል ከፍቅር እና ከትዳር መለያየት እንዴት እንደሚያስጠላ አስቡት። ግን እንዲህ የሚዋደዱ ከሆነ በምን ምክንያት ሊለያዩ ቻሉ። ልጁ ንግግሩን ቀጠለ።
"ያው የቤቱን እቃ ትቼላት ወጣሁ። ቴሌቭዥን ብትል አልጋ ሁሉንም ትቼላታለሁ እኮ!" እያለ ያወራል። ይሄ ጥል አይባልም ብየ አሰብኩ። ሰውን እየተዋደዱም ቢሆን የሚያለያየው ያ ገንዝብ የሚሉት ሰይጣን ነው ብየ እያሰብኩ እያለ
"እየውልህ እኔ ያ በረሃ የሆነን ቦታ ለእሷ ስል ነበር ተቋቁሜ የኖርኩት። አሁን ግን በቃኝ። ዘረኝነቷ አንገሸገሸኝ" ሲል ጆሮየን ማመን አቃተኝ። ከዚህ በላይ መስማት አልፈለኩም ያለ መንገዴ በቅያሱ ታጥፌ ሸሸሁት። ይሄ የዘረኝነት አባዜ ትዳር ውስጥም መግባቱ አበሳጨኝ። እግዜያብሄር በአምሳሉ የፈጠረውን ፍጡር ሰው መሆኑን ትተን ሰው ያለመሆን አባዜ ሲጠናወተን ራሴን መታኝ። አጥንት መቁጠር እዚህ ድረስ አጥንት ሰብሮ ይገባል። የማል!! ከክርስቶስ ፍቅርን እንማር። መልከም በዓል

Translate

Blog Archive

About Me