Search This Blog

Sunday 30 July 2017

8የደብረ ብረሀን ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች አባይ ባንኮችን ይሄዱና የደንበኞቻችሁን ገንዘብ የምታንቀሳቅሱበት ሲስተም ለዝርፊያ በቀላሉ ይጋለጣልና እኛ ደህንነቱን የሚያስጠብቅላችሁ ሲስተም እንዘርጋላችሁ ይሏቸዋል። "አሁን እናንተ.." በሚል አንፈልግም ይሏቸዋል። ልጆቹ "ለምን አናሳያችሁም" ብለው ሲስተሙን ሰብረው 80ሺ ብር አውጥተው ይጠቀሙበታል(ተመቹኝ)። በዚህ ምክንያት ልጆቹ በቁጥጥር ስር ዋሉ። እኔ ግን እነዚህን ልጆች ከማሰር እውቀታቸውን መጠቀም የሚሻል ይመስለኛል። በነገራችን ላይ ዩኒቨርሲቲው ውስጥ እሳት የላሱ ልጆች ሞልተዋል። አንደኛው ልጅ የግዕዝ አማርኛ መተርጎሚያ ሶፍትዌር አዳብሯል። ቀጣይ አመት ወደ ስራ ሊያስገባው እየሰራ ነው። ሌላው ደግሞ ከአፈር ኤሌክትሪክ ማመንጨት የሚያስችል ስራ ሰርቷን። አንዱ የፊዚክስ መምህር ደግሞ ሊባረሩ ጫፍ የደረሱ ተማሪዎችን ተቀብሎ በማስጠናት ለውጤት አብቅቶ ከልጆቹ ጋር በመሆን ከቆሻሻ ከሰል እያመረተ ነው።
ሌላ ደግሞ እዚያው ደብረ ብረሃን የሆነውን ልንገራችሁማ.....
ልጁ ሹፌር ነው። ማንም የሚቀጥረው ሰው ያጣል። በመሃል አባቱ በጠና ይታመማሉ። ስለዚህ ያለኝ አማራጭ ብር መስረቅ ነው ብሎ ወደ አካሉ ሆቴል ያመራል። ይገባና 11ሺ 300 ብር ይዘርፍና ሊያመልጥ ሲል ፓሊሶች ይከቡታል። ጥበቡን ተጠቅሞ ተሰወረባቸው። ፓሊሶቹ ሆቴል ገብተው ፍለጋውን አጧጧፉት። ልጁ የለም። ከደቂቃዎች ፍለጋ በኋላ አንደኛው ግድግዳው ጥግ ያለውን ነጭ ነገር ከፈተው። አጅሬ 11ሺ 300 ብሩን እና ቢራ ታቅፎ ከተጋደመው ፍሪጅ ውስጥ ጥቅልል ብሎ ተኝቶ ኖሯል። አስቡት በደብረ ብረሃን ብርድ ፍሪጅ ውስጥ ገብቶ በረዶ ሸፍኖት አለመጥፋቱ!? ልጁን ወዳጄ alayu geremew አግኝቶ ሲያናግረው "አባቴን ለማዳን ስል ስርቆት ውስጥ በመግባቴ እና ስሰርቅ በመያዜ አልፀፀትም" ብሎታል።

No comments:

Post a Comment

Translate

About Me