Search This Blog

Sunday 30 July 2017

"አንሶላ የተጋፈፍኳቸውን ሴቶች ቁጥር አላስታውስም። ቆንጆ ከሆነች እንድታመልጠኝ አልፈልግም። ሁሉም ቆንጆ ሴቶች ሚስቶቼ ቢሆኑ እመኛለሁ። በተለይ ይሄ የሹፍርና ስራየ ቀላል አልተመቸኝም። ማርሽ አስገብቼ እጄን ጋቢና ካስቀመጥኳት ልጅ ጭን ላይ ጣል አደርገዋለሁ። ዝም ካለች ጨዋታው ይቀጥላል። ካላለች ሌሎች ስልቶች ይከተላሉ።" አለኝ በታሪፍ ተጣልተን በኋላ ምርጥ ጓደኛሞች የሆንን አንድ ሹፌር። ጋቢና ሰው አለ ሲል ቆይቶ ሊሞላ አንድ ሰው ሲቀር ደርሼ ነው ያስገባኝ። "ምን እንደሚያስጠልኝ ታውቃለህ?" አለኝ።
"አላውቅም" አልኩት።
"ሌዘር የሚለብስና ሳምሶናይት ቦርሳ የሚይዝ ሰው" አለኝ። ፈገግ አልኩለት እና
"ለምን"አልኩት።
"በቃ አጉል መብቴ ይከበር ባይ ናቸው። የእኛ ስራ ውጣ ውረዱ አይታያቸውም። በጣም ስለሚያበሳጩኝ እንደዚያ ያሉ ሰዎችን አልጭንም" አለኝ።
"ስራችሁማ ምን ውጣ ውረድ አለው። የፈለካትን ሴት እያሳደድክበት.." አልኩትና ሳልጨርስ አቋረጠኝ
"እሱስ ልክ ነሽ አባየ! ስንቱን በላንበት መሰለሽ። ጥቅሙ ይሄ ብቻ ነው። እንጂማ ትራፊክ በያዘህ ቁጥር የቀን አበልህን ለመንግስት እየገበርክ እንዴት ትችለዋለህ?" አለኝ።
"ዛሬ ግን ጋቢና ቆንጆ ሴት ባለመጫንህ ቅር አላለህም?" አልኩት።
"ቀላል ብሎኛል! ሴቶች በጣም ነው ደስ የሚሉኝ። ደግሞ መሪ የያዘ ወንድ በጣም ይወዳሉ። እኔማ ጋቢና ሴት ካስቀመጥኩ ችግር አለብኝ። ለምን ትልቅ ሰው አትሆን መነካካቴን አልተውም። አንድ ግዜ ወደ ደሴ ስንሄድ መሽቶ ሁሉም ተሳፋሪዎች እንቅልፍ ያዛቸው። ጋቢና የተቀመጠችውን ሴት ነካክቻታለሁ። እጄን ማርሽ እየቀየርኩበት አስመስየ ጡቶቿን ሳይቀር አሸሁላት። እሷም የምትሆነውን አሳጣት። ቀስ ብየ መኪናውን ዳር አስይዤ አቆምኩትና ለሽንት እንደሚወርድ ሰው ወረድኩ። እሷም ገብቷታል ወረደች። በጀርባ በኩል ስዞር ሰዎቹ ከእንቅልፋቸው እየነቁ የመኪናው መቆም ግራ ገብቷቸው መጋረጃውን ገለጥ ገለጥ ማድረግ ጀመሩ። በብስጭት ገብቼ መኪናየን መንዳት ጀመርኩ" ብሎ መሪውን በመዳፉ መታ አደረገው። ሲያወራ እያዝናናኝ መጣ። ስሜቱን በጭራሽ መደበቅ አይችልም። ሲበዛ ግልፅ ነው። ወሬው ደግሞ ከሴትና ወንድ ወሬ እንዲወጣበት አይፈልግም።
"አንድ ግዜ ደግሞ ባልና ሚስቶች ኮንትራት አድርሰኝ ብለውኝ ጉዞ ጀመርን። ጋቢና መጥተው ሁለቱም ተቀመጡ። ልጅቷ እንዴታባቷ እንደምታምር አትጠይቀኝ። ረዳቴ ከኋላ ወንበር ሄዶ ተኝቷል። ቀኑ እየመሸ ሲሄድ ባልዮው እንቅልፍ አዳፋውና ከኋላ ልተኛ ብሎ ሄደ። ረዳቱ ቦታ ለቀቀለትና አስተካክሎ አስተኛው። ረዳቴ ጋቢና መጥቶ ልጅቷን መሃል አስቀምጥናት። አባየ.. ጨዋታው ተጀመረ። ልጅቷን ከጭኖቿ ጀምሬ ስደባብሳት ፈፅሞ ልትከለክለኝ አልዳዳታም። ረዳቴም ይነካካ ኖሮ ዝልፍልፍ ማለት ጀመረች። ቆይቼ ረዳቱን አስትቼ ነገሩን ጋብ አደረግንው። አንዲት ከተማ ደረስን። መኪናውን ጥግ አስይዘን እራት እንደሚበላ ሰው ሆቴል ገባን።.."
ወሬውን እንደቀጠለ ስልኬ ድንገት ጠራ። ይህንን እያወራኝ ስልክ አንስቶ ነገር ማቆርፈድ መስሎ ቢታየኝም የስራ ስልክ ስለሆነ ማንሳት ግዴታ ሆነብኝ።
"ሄሎ"
"ደህና ዋልክ አዲስ ማታ ስራ መግባት አለብህ" ተባልኩ። መመለስ አለብኝ ማለት ነው።
"ሹፌር ስራ ገጠመኝ ወደ አዲስ አበባ ልመለስ ነው። መኪና አስቁምልኝ" አልኩት። መኪና አስቁሞልኝ ወደ አዲስ አበባ ጉዞየን ጀመርኩ። የልጁ ድርጊት ግን ከአዕምሮየ ሊወጣ አልቻለም።...

No comments:

Post a Comment

Translate

About Me