Search This Blog

Sunday 30 July 2017

አብዲሳ አጋ

እጅ እና እግሬን የፊጥኝ አስረው ከፎቅ ላይ ወረወሩኝ። በታዕምር ተረፍኩ። ፓሊስ ጣቢያ ወሰዱኝ። ውሃ በላየ ላይ እያፈሰሱ እስኪበቃቸው ደበደቡኝ። ውሃውን በላየ ላይ ለቀውት ሲፈስብኝ አደረ።በዚያ ላይ መሬቱ ሲቢንቶ ነበር። ጠዋት ሲመጡ "ይሄ ጥቁር አልሞተም" ብለው በመስኮት አይተውኝ ይሄዳሉ። የህዝቡ መገደል የአላግባብ ደም መፍሰስ ያሳዘነኛል። ይቆጨኛል። ከአዲስ አበባ ሞቃዲሾ፤ ከሞቃዲሾ ጣልያን ናፓሊ በመርከብ ነው የሄድንው። ናፓሊ ውስጥ አኛ የሚባል እስር ቤት ገባን። ተለይቶ የተዘጋጀ ቦታ ነው። እዚያ ሆነን የእንግሊዝ መንግስት ወረቀት ይበትን ነበር። የእነ ሃይለስላሴን፣ሩዝቬልት፣ናፓሊን እና የመሳሰሉትን መሪዎች ስም የያዘ ነው። ይህንን ወረቀት ይዟል ተብየ ሰደበደብ መሞቴ ካልቀረ ብየ ወታደሩን መልሼ መታሁት። ይሄ ነው ከፍተኛ ድብደባ የዳረገኝ።
ስር ቤት እያለሁ ለማምለጥ ከፍተኛ ጉጉት ነበረኝ። ጁሌት የሚባል ዩግዝላቪያዊ ጓደኛየም ይህንን ያስብ ኖሯል። 3ኛ ፎቅ ላይ ነበር የታሰርኩት። አንድ ቀን አቅሮፕላን መጥቶ ሲደበድብ አጋጣሚውን አግኝተን በመብራቱ ታግዘን ከ3ኛ ፎቅ ብርድ ልብስ ቀድጄ በእሱ ወርጄ ከጄሌት ጋር አመለጥን። ወደ ሳንቢችኖ ተራራ ለመድረስ ስንጓዝ አደርን። በማግስቱ ደረስን። በኋላ እንግሊዛዊው አዛዥ ሜጄር ፋይልን
"እዚያ ብዙ ኢትዮጵያኖች እና ዩጎዝላቪያን እስረኞች አሉ እነሱን ማስፈታት እንፈልጋለን። እነሱን እናስለቅቅና መሳሪያም እንዝረፍ " ብለን መሳሪያ እንዲሰጠን ጠየቅን።
" ይሄ ይፈፀማል ብየ አለምንም ግን ውሰዱ" ተብለን ተፈቀደልን። እዚያ ከነበሩት ኢትዮጵያዊያን እንግሊዛዊያን እና ዩጎዝላቪያን ውስጥ 30ዎቹ ወደ እስር ቤት ሰበራው ለመሄድ ተስማሙ። እጃችን ላይ የነበረው መሳሪያ 1ሳንጃ፣ አንድ አልቤን ክላሽ፣አንድ የእጅ ቦንብ እና 2ክላሽ ነው። እስር ቤቱ 75ኬ.ሜ አካባቢ ይርቃል። እስር ቤቱ ለመድረስ ትንሽ ሲቀረን እና ትሬያ የምትባል ከተማ ስንደርስ ስልክ እና መብራት እንዲቆረጥ አደረግን። እስር ቤቱ ደረስን። እኔ እና ዱገላስ በደረታችን ተስበን ወደ ዘቡ ስንጠጋ ዘቡ በቁሙ እንቅልፍ ይዞት አየን። ዱገላስ በተክለ ሰውነት ገዘፍ ስለሚል አንገቱን ሲይዝልኝ እኔ ጠመንጃውን እና እግሩን ይዤ ወደ ጉድጓድ ውስጥ ወስደን ገደልንው። ዱገላስ የዘቡን ልብስ ለብሶ እንዲቆም አደረግን። ሌላ ዘብ ደግሞ ለቅያሬ መጣ። ያንንም ዘብ ገላገልንው። ሌላኛውን ዘብ ያዝንና መሳሪያችንን ወደ 3 ከፍ አደረግንው። ዘብ ቤት ሄደን የሁሉንም መሳሪያ ወሰድን። አንደኛውን ዘብ "የወህኒ ቤቱ ሃላፊ ወዳለበት ቦታ ውሰድን" አልንው። አማራጭ ስላልነበረው ወሰደን። ማርሻል ሎጄስቴሬኢያሪኮ ይባላል።
"ማርሻል" ብሎ ተጣራ።
"አቤት" አለው
"ከታች ብዙ ድምፅ ይሰማኛል ምንድነው?" አለው
"መብራትም ጠፍቷል ምን ይሆን" ብሎ ተነሳ። ብቅ ሲል በመትረየስ መታሁና ጣልኩት። ሚስቱ እና ልጆቹ መንጫጫት ሲጀምሩ እነሱንም ጭረስናቸው። እስረኞቹን በሙሉ አስፈታናቸው። ምግብ፣ ልብስ እና በርካታ መሳሪያዎችን ዘረፍን እና መሄድ የፈለጉትን እስረኞች ይዘን ወደ ቦታችን ተመለስን።
.....አንድ ቀን የጀርመን ናዚ ወታደሮች በአውሮፕላን እኛ ከሰፈርንበት ቪያኖራ ቦታ አረፉ። ቦታውን ለመሰለል ኖራል የመጡት። አንዱን ያዝንው እና ሁሉቱን አውሮችላናቸውን አስነስተው አመለጡን። የተያዘውን ሰው ምርመራ አደረግንበት።ዮጎዝላቪያዊው ሜጀር ጁሌት ጀርመንኛ ጥሩ አድርገጎ ይናገር ስለነበር የመጡበትን ምክንያት ጠየቀ።
"እዚህ ቦታ አርበኞች ስላሉ እነሱ ያሉበትን ቦታ አይተን በሌላ ግዜ በእግረኛና በአውሮፕላን ለመደብደብ ነው ብሎ" ይመልሳል። "ይሄ ፍርድ ያስፈልገዋልና ፍርድ መሰጠት አለበት" ብለን ወሰንን። እንግሊዛዊው ሜጀር ፋይል እንዲደበደብ አዘዙ። የምትፈልገውን ተናገር ሲባል
"አንደኛ በሌላ ሰው እጅ እንዳልደበደብ በኢትዮጵያዊው አንቶኒ(አብዲሳ) እጅ መሞት እፈልጋለሁ።ሁለተኛ መሳሪያየን ለእሱ መታሰቢያ ስጡልኝ" ብሎ ተነገረ። ከዚያ ደግሞ "አንድ ቃል ልናገር ብሎ መንግስቴ ለዘላለም ይኑርልኝ" ብየ ልናገር ብሎ ተፈቀደለት።
..... ድል አድርገን ሮም ስንገባ 400 ወታደሮች ሁሉም የውጭ ሃገር ዜጎች ናቸው የእንግሊዝን ባንዲራ በቀኝ ክንዳቸው የኢትዮጵያን ባንዲራ በግራ ክንዳቸው ላይ እንዲያስሩ አደረኩ። እኔ የምፈልገው የኢትዮጵያ ቀለም እዚያ መገኘቱን ነበር።
..... እዚያ በእኔ ስም ሽፍቶች ሃገሬውን ይዘረፉ ነበር። ተከታትየ በህይወታቸው ቀጣኋቸው።
...... እዚያ ሆኜ እናቴም አባቴም ወንድሞቼም አይደሉም የሚናፍቁኝ። ሃገሬ ብቻ ነበረ የሚናፍቀኝ። ሃገሬ ነው
አብዲሳ አጋ ከኢትዮጵያ ራዲዩ ጋር ካደረጉት ቃለመጠይቅ የተወሰደ

No comments:

Post a Comment

Translate

About Me