Search This Blog

Friday 17 June 2016

"የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ. ደጋፊ ስለሆንሽ ቤቴን ልቀቂልኝ" ተባልኩ
@@@@@@@@@@
እኔ የምለው በቃ በልዩነት መኖር አንችልም ማለት ነው? ልዩነት
ውበት ነው የሚባለውስ አባባል ለፖለቲካ አይሰራም ማለት
ነው? የኢህአዴግ ደጋፊዎች የተቃዋሚ ደጋፊዎችን በጣም
ይጠላሉ። የተቃዋሚ ደጋፊዎች ደግሞ የኢህአዴግ ደጋፊዎችን
አምርረው ይጠላሉ። የፖለቲካ አቋም ልዩነት ጥላቻ ላይ ሲደርስ
ማየት ያስጠላል። ማንም ሰው የኢህአዴግ ደጋፊ እንደሆነው
ሁሉ የተቃዋሚ ደጋፊም መሆን መብቱ ነው። በተቃራኒው
የተቃዋሚ ደጋፊ እንደሆነው ሁሉ የመንግስት ደጋፊም መሆን
መብቱ ነው። እርስ በእርስ ግን ጥልቅ ጥላቻ ውስጥ መግባት
ልዩነትን ያለመቀበል ችግር ነው። የእኔን አስተሳብ ይዘህ ኑር፤
እኔ አውቅልሃለሁ የሚል እሳቤ ስለ እውነት ያናድዳል። እርስ
በእርስ ስንወነጃጀል ያለ ለውጥ ሲባሉ መኖር! ወደ ነገሩ
ልግባማ። አንድ ወዳጃችን አከራዮቿ "ቤቱን ልናድሰው ነው"
ብለዋት ቤት እንደምትፈልግ ስትነግረን ወራት አልፈው ነበር።
በመካከል ቤቱን እየፈለግንላት ብናይም ብናይም ቤቱ
አይታደስ። "ቤት አገኘሽ?" ትላታለች አከራዮዋ።
"ቆይ ገና ነኝ።እድሳት እስክትጀምሩ ማግኘቴ አይቀርም"
ትላቸዋለች። እስኪታደስ ድረስ ዝም ብላ መኖሯ ነው ብላ ነው
መስለኝ ትላንት አከራዩዋ እንቅጩን ነገረቻት።"ቤቱን ልናድሰው
ነው ያልንሽ ውሸታችንን ነው። ጋዜጠኛ እና የኢህአዴግ ደጋፊ
ስለሆንሽ እናንተን ማከራየት ስለማንፈግ እንድትለቂ ነው"
አለቻት። በጣም ያዘንኩት በጥላቻ ለተሞላው ፖለቲካችን ነው።
ሲጀመር እነሱ መንግስትን እንደሚቃወሙት ሁሉ እሷም
መንግስትን የመደገፍ መብት አላት። ብቻ በነገሮች አዘንኩ።
ሳስበው ግን እንዲህ ያለ አሰተሳሰብ እንዲመጣ ያደረጉት
ራሳቸው የኢህአዴግ ደጋፊዎች ናቸው። 97 ላይ የቅንጅትን
ደጋፊ ለምን ቤት አከራያችሁ ተብለው የተወቀሱ አከራዮች
እንዳሉ አውቃለሁ። ይሄው ነገሩ ተገለበጠ እና እርፍፍ።

No comments:

Post a Comment

Translate

About Me