Search This Blog

Wednesday 8 June 2016

የፍርሃት ቆፈን

የፍርሃት ቆፈን በተመስገን እህት አዕምሮ ውስጥ
@@@@@@
ያቺን የቡና ሱሴን ለማሟላት ከሰፋራችን ካለች ምግብ ቤት ጎራ
አልኩ። ቤቷ ትንሽየ ብትሆንም ቡና፣ የአልኮል መጠጥ እና
ምግብም ይሸጥባታል። ከሰል ምድጃው ላይ የተጣደውን ጀበና
አይን አይኑን ሳይ የሆኑ ጥቁር ወፍራም ሴትዮ መጡና ከፊት
ለፊቴ ቢራ ከሚጠጡት ወንዶች ጋር ተቀላቀሉ። ወዲያው ነው
ቢራ የተሰጣቸው። ወንዶቹ በአካባቢ ይነቋቆራሉ። ጎጃሜ እና
ጉራጌ በንግድ ፣ ጎንደሬ በሰሊጥ፣ ሸዋ.... ምናምን እያሉ
ይሽካካሉ። ሴትዮዋ ሲገቡ ትንሽ ተሳሳቁና ነገሩን ወደ ጭቅጭቅ
ቀየሩት። 3ቱም ወንዶች ሴትዮዋን በነገር ያዋክቧቸው ጀመር።
አንዱ፦ "በምን እናውቀለን የእሱ እህት መሆንሽን? ሰው ታዋቂ
ሰው እየፈለገ እህቴ ነው፣ ወንድሜ ነው ፣የአጎቴ ልጅ ነው
፣ምናምን እያለ ሆዳችንን ይነፋዋል።"
ሴትዮዋ፦" እሱም እንደ እኔ ጎራዳ ባሪያ ነው።"
ሌላኛው፦ "አናምንሽም ባክሽ።"
ሴትዮዋ በጣም እየተበሳጩ መጡ።
አንደኛው፦ ወንድምሽ ተው አትፃፍ ይቅርብህ ሲባል ነው ከርቸሌ
የተወረወረው ።አልሰማ ብሎ። ደግሞ ምን ጎደለበትና ነው
መንግስትን የሚቃወመው? ድልድይ ተሰራ፣ መንገድ ተሰራ ፣
ይሄው አሁን ደግሞ አባይ ሊገደብ ነው። ምን ልሁን ብሎ ነው?
" አላቸው።ከት ብሎ ይስቃል።
ሴትዮዋ ገልመጥ ገልመጥ ማለት ጀመሩ።
ያኛው፦ ተናገሪ እንጂ ምን ያስፈራሻል?
ሴትዮዋ፦ የእኔ ወንድም ነግሯቸዋል። እኔ ሌባ አይደለሁም።
በፊት ግን አዎ ቸግሮኝ እሰርቅ ነበር ብሏቸዋል። ብለው
ያልተወራ ቀላቀሉበት። ከጎናቸው ላለው ወጣት የሆነ ነገር ሹክ
አሉት።
ሰውየው፦ "አይዞሽ ማንም አትፍሪ። ማንም አይናገርብሽም። ቆይ
ግን ትፈሪያለሽ እንዴ? " አላቸው
ሴትዮዋ ፦ "እንዴት አልፈራም?"ብለው መለሱ።
-ይህን ግዜ እሱ ቢሆን ከየትም ከየትም ብሎ ምላሽ አያጣም
ነበር"ብሎ ወደ ውጭ ወጣ።ከጎኔ ያለው ሰውየ ወደ ጆሮየ ጠጋ
ብሎ
- ተመስገንን ታውቀዋለህ?" አለኝ
- ተመስገን የቱ? ብየ ጥያቄውን በጥያቄ መለስኩለት።
-ተመስገን ደሳለኝ ጋዜጣ ላይ ይፅፍ የነበረው።"
- አዎ አውቀዋለሁ።
- "የእሱ እህት ናት። የታሰረ ሰሞን እስር ቤት ሄዳ ገርፈውት
አይታው እንደዚህ ንክ ሆና ቀረች" አለኝ።አሁን የፈለጋትን ነው
የምትናገረው ግን ስትፈራ አይጣል" አለኝ።ሴትዮዋን አየኋቸው
ድጋሚ ቢራ አዘዙ።
"በጥይት ቢመቱት እዳው ብዙ ነው፤
በለው በእስኪብርቶ ሰንበር በሌለው።" የሚለውን ግጥም
ገልብጨ ገጠምኩት።

No comments:

Post a Comment

Translate

About Me